የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ መክፈቻ በምሕላ ጸሎት ተጀመረ

 

 

ጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. 

በእንዳለ ደምስስ

የጥቅምት 2006 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው እለት ጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ ዐሥር ሰዓት ጀምሮ ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳምabatoch በምሕላ ጸሎት ተጀመረ፡፡

 

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ በሚያካሒደው ስብሰባ ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡