መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የቅዱሳን መላእክት አማላጅነት
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁልን?! በፈቃደ እግዚአብሔር አዲሱን ዓመት ከተቀበልን ሁለት ወራትን አሳልፈን ሦስተኛውን ጀምረናል! ለዚህ ያደረሰን አምላክ ይመስገን! ለመሆኑ ትናንት ከነበረው ማንነታችሁ ላይ ምን ለውጥ አመጣችሁ? በዘመናዊ ትምህርትስ ምን ያህል ዕውቀትን ሸመታችሁ? በመንፈሳዊ ሕይወታችሁስ በሥነ ምግባር ምን ያህል ለውጥ አመጠችሁ? በርትታችሁ መማር ይገባል፤
….ባለፈው ተከታታይ ትምህርታችን ስለ አማላጅነት ትርጉም እንዲሁም ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ተምረን ነበር፡፡ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ ስለ ቅዱሳን መላእክት አማላጅነት እንማራለን! መልካም!
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎችን የሃይማኖት ነጻነት የሚጋፋ መመሪያ ማውጣቱ ተገለጸ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን የሚጋፋ መመሪያ መውጣቱን ገለጹ፡፡ ዮኒቨርስቲው በ፳፻፲፯ ዓ.ም ያወጣውን የሥነ ምግባርና ዲሲፕሊን መመሪያ ተከትሎ ይህንን መመሪያ ማውጣቱን ተማሪዎቹ አክለው ገልጸዋል፡፡
እኔም ልመለስ!
እኔም ልመለስ ድንግል እናቴ
ከስደት ሕይወት ከባርነቴ
በልጅሽ ጉንጮች በወረደ ዕንባ
ባዘነው ልብሽ በተላበሰው የኀዘን ካባ
በእናት አንጀትሽ እንስፍስፍ ብሎ ያኔ በባባ
ልመለስ ድንግል ሆይ እኔም ከስደት
እውነትን ልያዝ ልራቅ ከሐሰት፡፡
ጥላቻ ገዝቶኝ ወንድሜን ከጠላው
እምነት ምግባሬን ሰይጣን ዘረፈው
መልሽኝ ድንግል ይብቃኝ ግዞቱ
በምግባር እጦት በቁም መሞቱ!
ወርኃ ኅዳር
ሦስተኛው ወር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት “ኅዳር” ተብሎ ይታወቃል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል ሲተረጉሙ “ማኅደር” ከሚለው ሥርወ ቃል የወጣ እንደሆነና “ማደሪያ” የሚል ፍቺ እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? በርትታችሁ እየተማራችሁ ነውን? ጥናቱንም ከወዲሁ ጀምሩ! አዲሱን ዓመት ከተቀበልን ሁለት ወራትን አስቆጥረናል፤ ታዲያ በእነዚህ ጊዜያት በዘመናዊ ትምህርታችን ከነበረን ዕውቀት ምን ያህል አዲስ የማናውቀውን ነገር ዐወቅን? አንዳንድ ትምህርት ቤት የሙከራ ፈተና ጀምረዋል፤ ታዲያ እንዴት ነበር የመመዘኛው ፈተና? ጥሩ ውጤት እንዳስመዘገባችሁ ተስፋችን ነው! መልካም!
ባለፈው ትምህርታችን ስለ አማላጅነት በመጠኑ ተምረናል፤ ለዛሬ ደግሞ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት እንማራለን፤ ተከታተሉን!
ከውድቀት አነሣን!
ለሰሚው በሚከብድ ቃላት በማይገልጸው
በመከራ ውሎ አዳምን አዳነው!
ዲያብሎስ ታሠረ አዳም ነጻ ወጥቶ
ልጅ ተባለ ዳግም በደሉ ተረስቶ
የማይሞተው አምላክ ስለ እኛ ሲል ሞቶ
ከውድቀት አነሣን ልጅነትን ሰጥቶ!
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ አምስት ቁጥር ፻፷፬ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት ፲፩ እስከ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡
‹‹በጎውን ማን ያሳየናል የሚሉ ብዙዎች ናቸው›› (መዝ.፬፥፮)
እንደዚህ እንደኛ ያለ ክፉ ዘመን የገጠማቸው፣ መጥፎውን ትቶ በጎውን፣ ጠማማውን ሳይሆን ቀናውን፣ የጨለማውን ሳይሆን የብርሃኑን ጎዳና የሚያሳያቸው፣ የሚነግራቸውና የሚያስተምራቸው ያጡ፣ ግራ የተጋቡ ሕዝቦችን የተመለከተበትን ነገር እየነገረን ይመስላል ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው ይህንን ኃይለ ቃል የነገረን፡፡
“የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል” (ማቴ.፳፬፥፯)
የምድር መናወጥ ወይም መንቀጥቀጥ በታሪክ መመዝገብ ከተጀመረበት ዘመን አንሥቶ እስከደረስንበት ዘመን ድረስ ከባድ የሚባል በሬክተር ስኬል ሰባት ነጥብ ሁለት እና ከዚያ በላይ በዐሥርት ዓመታት ቢበዛ አንድ ጊዜ ነበር የሚከሠተው፡፡ ከ፲፱፻ ዓ.ም ወዲህ ግን ክብደቱም ብዛቱም የሚያደርሰውም ሰብአዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊና መሠረተ ልማታዊ ውድመቱና ጥፋቱ ጨምሯል፡፡ ከ ፲፱፻ እስከ ፲፱፻፵፱ በየዐሥርት ዓመቱ የሚደርሰው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ሦስት እና ከዚያ በላይ ሆኗል፡፡ በ፲፱፻፶ዎቹ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሮ ዘጠኝ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ በ፲፱፻፸ዎቹ ፻፳፭ አደገኛ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ ይህንን ሁኔታ ስንመለከተው ምድራችን በመሬት መንቀጥቀጥ ብዛትና ክብደት እየፈረሰች መሄዷ የማይቀር መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
የዛፉ ፍሬ
አዳም ያየ መስሎት ዓይኑ እንደተዘጋ
ይኖር ነበር ገነት ብቻውን ሲተጋ
ሔዋን ባትቀጥፈው የበለሱን ፍሬ
መቼ ይሰማ ነበር የአምላክ ልጅ ወሬ
አዳም የተከለው የፍቅር አበባ አድሮ እየጐመራ
አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን አብቦ ቢያፈራ
ከላይ ከሰማያት መንበረ ጸባኦት
የአምላክን አንድ ልጅ መዓዛው ጐትቶት