መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




ነገረ ጳጕሜን
ኢትዮጵያ የራሷ ባህል፣ ታሪክና ሃይማኖት ያላት ይህንም በትውፊትና በመጽሐፍ ቅዱስ ይዛ የቆየች ሀገር ናት፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው ውሸት ቢናገርና በውሸታሞች መካከል ቢደገፍ ሌሎችም ውሸት ይናገሩ እንደማይባል ኢትዮጵያም ሌሎች በንጉሣቸው በጣዖታቸው ስም በየጊዜው እየቀያየሩ የዘመን ቆጠራን ቢያከብሩ የራሷን እውነት ትታ የእነርሱን ውሸት ትቀበል እንደማይባል መረዳት ይጠይቃል።
የቱን ታስታውሳላችሁ?
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በየዓመቱ በጉጉት የምጠብቃት ጾመ ፍልሰታ እንዴት አለፈ? እንዴት አቅማችን በመጾም፣ በመጸለይ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤዛዊት ዓለም በረከትን ተቀብለን እንዳለፍንበት ተስፋችን እሙን ነው፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ከጾመ ፍልሰታ በፊት “የቱን ታስታውሳላችሁ?” በሚል ርእስ ስንማራቸው ከነበሩ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር መካከል የተወሰነ ጥያቄዎችን ጠይቀናችሁ እናንተም ምላሹን ልካችሁልን ነበር፤ ለጥያቄዎቹ ተገቢውን ምላሽ ለሚሰጡም እንደተለመደው ሽልማቶችን እንደምናዘጋጅ ነግረናችሁ ነበር፡፡ የሽልማት መርሐ ግብሩን በተለየ መርሐ ግብር እናዘጋጃለን፡፡
በእንተ ዕረፍቱ ለተክለ ሃይማኖት
የስሙ መነሻ ፊደሉ ትእምርተ መስቀል የሆነው፣ የወንጌል ተቀዳሚ ስም ማቴዎስ፣ የቅዱስ ወንጌል ጸሐፊዋና ሰባኪዋ ማርቆስ፣ የነፍስና የሥጋ ሐኪም ሉቃስ፣ ከሁሉ ይልቅ ሥልጣኑ ከፍ ያለ ጴጥሮስ፣ ሰማያዊ አርበኛ ሚናስ፣ አነዋወሩ በብቸኝነትና በንጽሕና የሆነ ኤልያስ፣ የቤተ ክርስቲያን የልጆቿ አባት ባስልዮስ፣ የቤተ ራባው ጸዋሚ ተሐራሚ ዮሐንስ፣ ዐሥረኛው የአርማንያው ጎርጎርዮስ፣ ግሙደ እግር ያዕቆብ ሐዋርያ፣ እንግዳ መቀበል ፍጹም ተግባሩ የሆነ አብርሃም፣ ጸሐፊ ምሥጢራት ወጥበባት ሄኖክ፣ መሥዋዕቱ የሠመረለት አቤል፣ ሕዝብን የሚያስተዳድር ዮሴፍ፣ እግዚአብሔርን በንጹሕ ልቡና የሚያመሰግን ዳዊት፣ ከሐዲዎችን የሚበቀል ቄርሎስ፣……………..
‹‹እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?››
ከነገደ ብንያም የተወለደው ነቢዩ ሚክያስ የስሙ ትርጓሜ ‹‹እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?›› ነው። እንደ ስሙ ትርጕምም የእግዚአብሔር ቸርነት ከየትኛውም ኃጢአትና ከየትኞቹም በቊጥር የበዙ ኃጢአተኞች ይልቅ ታላቅ መሆኑን፣ ይልቁንም እግዚአብሔር ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኞችን የማይጸየፍ እንደሆነ አስተምሯል። በሰባት ምዕራፎች በተጠቃለለ ነገረ ድኅነትንና ንስሐን ማዕከል ያደረገ ትምህርቱና ትንቢቱ መሲሑ የሚወለደበትን ስፍራ ሳይቀር ‘ደረቅ ትንቢት’ በግልጽ እንዲህ ሲል “አንቺ ቤተልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘለዓለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል” ተናግሯል።
በእንተ ስምዐ ለማርያም
ዛሬ በፍልሰታዋ በአዛኝት የጾም ወራት
ልመናዬ አይደለም ፍርፋሪ ኩርማን ዱቄት
በደብረ ታቦሩ በዓል በተገለጸበት ምሥጢር
የዕለት ጉርሴን አልጠይቅም ቆሜ በደጅዎ በር
ልለምን . . . በእንተ ስማ ለማርያም
ስለ ወላዲተ አምላክ . . .
ወርኃ ነሐሴ
ነሐሴ የሚለውን ቃል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ላይ “ናሴ” ማለት መጨረሻ የመስከረም ዐሥራ ሁለተኛ በማለት ይፈቱታል፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝመበ ቃላት ገጽ ፮፻፴፯)
የቱን ታስታውሳላችሁ?
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና ዕርገት መታሰቢያ ለሆነው ጾመ ፍልሰታ አደረሳችሁ፡፡ ልጆች! በየዓመቱ በጉጉት የምንጠብቃት ጾመ ፍልሰታን እንደ አቅማችን በመጾምና በመጸለይ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤዛዊተ ዓለም በረከትን መቀበል ይገባናል፤ ልጆች! በጾመ ፍልሰታ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ፣ ትምህርት በመማር፣ በማስቀደስ፣ መልካም ምግባራትን በመፈጸም መሳተፍ አለብን፡፡
ልጆች! በዛሬ “የቱን ታስታውሳላችሁ?” መርሐ ግብራችን ባሳለፍነው ዓመት ስንማራቸው ከነበሩ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባራት መካከል የተወሰነ ጥያቄን አዘጋጅተንላችኋል፡፡ ከዚህ ቀደም የአስተማርናችሁን ትምህርት በደንብ ከልሷቸው፤ ከዚያም ለጥያቄዎቹ ተገቢውን ምላሽ በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ! እንደተለመደው ጥሩ ውጤት ለሚያመጡ ልጆች ሽማቶችን አዘጋጅተናል፡፡
ተጠያቂው ማነው?
መምሬ እውነቱ ከንስሓ ልጆቻቸው ጋር በመሆን ሕሙማንን ለመጠየቅ በያዙት መርሐ ግብር መሠረት ከምእመናኑ ተወካዮች እና ከማኅበረ ካህናቱ ተወካዮች ጋር የተቃጠሩበት ሰዓት እስኪደርስ ከግቢያቸው ካለው ዛፍ ሥር ተቀምጠው ሌሎቹን በመጠበቅ ላይ ናቸው፡፡
የቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ካርታ
ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንደምን ሰነበታችሁ? የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የተመሰገን ይሁን! ባለፈው ክፍለ ጽሑፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የመጪው ዐሥር ዓመታት የመንፈሳዊ እና ዘላቂ ልማት ግቦችን ማስተዋወቅን ዓላማ አድርገን፣ በክፍል አንድ ስለ ፍኖተ ካርታ (ዕቅድ)፣ በክፍል ሁለት ደግሞ ከዋና ዋና ዘርፎች በመንፈሳዊ ዘርፍ የተዘረዘሩ ግቦችን አቅርበንላችሁ ነበር፡፡ በክፍል ሦስት ደግሞ ቀጣዩን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
ስማችን!
ሕፃን ሆኖ አባቷ፣ አባት ሲሆን ልጇ
በእምነት ያበረታት ወርዶ ከእቅፍ እጇ
ወደ ሞት እንዳትሄድ ሥቃይን ተሰቅቃ
ለልጄ እንዳትል የመከራ እሳት ሞቃ
ቆሞ መሰከረ ድምጹን አሰምቶ
ከአላዊው ንጉሥ በመንፈስ ተሞልቶ