መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ቁጣና መዘዙ
ቁጣ የሚጫር የእሳት ክብሪት ማለት ነው፡፡ እሳት አንድ ጊዜ በክብሪት ከተጫረች በኋላ ሰደድ እሳት ትሆናለች፡፡ በቁጣ ሁሉም የኃጢአት ዓይነቶች ከመዛግብቶቻቸው ወጥተው ይቀጣጠላሉ፡፡ አንድን ሰው ድንገት አንድ ቁጡ ሰው ተነሥቶ ክፉ ቢናገረውና በይቅር ባይነት መንፈስ ቢያልፈው እንኳን ያ ቁጡ ሰው ቀኑን ሙሉ በቁጣ ላይ ሠልጥኖ ይውላል።
“ሰው ችግሩን በልቡ እያወቀ በዓይኑ እያየ እንዴት ገደል ውስጥ ይገባል? ዕርቅና ይቅርታ ማንን ጐዳ? ሰላምና አንድነት ማንን አከሰረ? ሰበብ አስባብ እየተፈለገ በሆነውም ባልሆነውም ከመተላለቅ ለምን ኢትዮጵያ የሁላችን ናት ብለን በእኩልነትና በስምምነት መኖር አቃተን?”
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ በዓለ ልደትን አስመልክቶ ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ያስተላለፉት መልእክት።
ወልድ ተወለደልን!
ኧረ ይህች ቀን ምንኛ ድንቅ ናት!
በዓይን የማይታየው የተገለጠባት
የማይዳሰሰው በአካል የተገኘባት
አንድ አምላክ ፈጣሪ የተወለደባት
እርሱ ነው ተስፋችን የዓለም መድኃኒት
የሆነው ቤዛ ለሁሉ ፍጥረት!
ወልድ ተወለደልን መድኃኒዓለም
በከብቶች በረት በቤተ ልሔም!
‹‹ወደ ቤተ ልሔም እንሂድ!›› (ሉቃ.፪፥፲፭)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! ትምህርት እንዴት ነው? አሁንማ ፈተና ደርሷል አይደል ልጆች? ስለዚህ ጨዋታ ሳያታልላችሁ በትኩረት በማጥናት፣ ያልተረዳችሁትን በመጠየቅ፣ የግማሽ ዓመት ፈተናውን በጥሩ ውጠየት ለማለፍ ማቀድ አለባችሁ!
ታዲያ በቀደሙት ትምህርታችን ስለ ጾመ ነቢያትና ስለ ነቢያት አባቶቻችን ስንማማር ነበር፤ አሁን ደግሞ የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እናከብራለን፤
መልካም አስተዳደር እና ቤተ ክርስቲያን
የእግዚአብሔር ቤተ ሰቦች! እንዴት ሰነበታችሁ? በክፍል ሁለት ጽሑፋችን ‹‹የቤተ ክርስቲያን መልካም አስተዳደር እጦት መንሥኤዎች›› በሚለው ርእስ ከተራ ቁጥር አንድ እስከ አምስት የዘረዘርናቸውን ምክንያቶች ታስታውሳላችሁ፡፡ በዚህ ክፍልም ከዚያው የቀጠለውን ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ!
ሰባቱ ኪዳናት
ኪዳን በሰውና በእግዚአብሔር እንዲሁም በሰውና በሰው መካከል የሚመሠረት ስምምነት ነው።ዋናው ጉዳያችን እግዚአብሔር ከፍጥረቱ ጋር የሚያደርገው ቃል ኪዳን ነው። በባሕርይ የማይታየው እግዚአብሔር ምሕረቱ የበዛ ስለሆነ ብዙ ጊዜ ከፍጥረቱ ጋር መሐላ ፈጽሟል። ከብዙ አበው ጋርም ቃል ኪዳን አድርጓል። የማይታይና ኃያል እግዚአብሔር ከፍጥረቱ ጋር የሚያደርገውን ውል ለተመለከተ ቸር አምላክ እንዳለው ያውቃል።
የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን
ጾም፣ ጸሎት፣ ምጽዋትና ስግደት መንፈሳዊ ትጥቆችና ሥጋችንን ለነፍሳችን እንዲሁም ለእግዚአብሔር የምናስገዛበት መንገዶች ናቸው!
ልደተ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
እንኳን ከጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ልደት በዓል በሰላም አደረሰን!
የልደቱም ነገር እንዲህ ነው!….
በዓለ ቅዱስ ገብርኤል
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ሳምንቱ እንዴት አለፈ? በሰንበት ቤተ ክርስቲያን ሄዳችሁ መንፈሳዊ ትምህርት እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋችን እሙን ነው፤መልካም! ለዛሬ ልንነግራችሁ የተዘጋጀነው ቅዱስ ገብርኤል ከእሳት ስላዳናቸው ሦስቱ ሕፃናትና እና ይህን በዓል አስመልክቶ ክብረ በዓል ከሚከበርባቸው ቅዱሳን መካናት መካከል አንዱ ስለ ሆነው ስለ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ነው!
መልካም አስተዳደር እና ቤተ ክርስቲያን
መልካም አስተዳደር ምን ማለት እንደ ሆነ ከዚህ በፊት ባቀረብነው ክፍለ ትምህርት ለመግለጽ ሞክረናል፡፡ ለቤተ ክርስቲያን አስፈላጊ መሆኑ እንደማያጠያይቅም ተመልክተናል፡፡ ይሁን እንጂ ቤተ ክርስቲያናችንን ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከመመሪያ እስከ አጥቢያ የመልካም አስተዳደር እጦት በእጅጉ እየፈተናት መሆኑን በርካታ አካላት ይገልጻሉ፡፡