New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

«ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ» ማቴ. 11፥28

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

እግዚአብሔር ሁሉን አዘጋጅቶ በመጨረሻ ለፈጠረው ለሰው ልጅ ያላደረገለትና ያልሰጠው ነገር የለም፡፡ ሁሉን ከማከናወኑ ጋር የሰው ልጅ የሚያስፈልገውን ነገር በአባትነቱ ያውቃልና የሰው ልጅ በባሕርይው የሚያሻውን ነገር የሚያበጃጃት ገነት፣ የምትመቸውን ረዳት፣ የሚገዛቸውን ፍጥረታት ሁሉ ለሰው እንደሚገባ ሰጥቶታል፡፡ ከእነዚህ ተቆጥረው ከማያልቁ ሥጦታዎች አንዱ ደግሞ ዕረፍት ነው፡፡ «እግዚአብሔር የተናገረው ይህ ነው፤ ነገ ዕረፍት ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ሰንበት ነው» ተብሎ እንደተጻፈ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ዕረፍት እንደሚያስፈልግ አውቆ የሰንበትን ቀን ሰጥቶአል /ዘጸ. 16.23/፡፡

«ሠርዐ ለነ ሰንበተ ለዕረፍተ ዚኣነ ፍስሓ ወሰላም ለእለ አመነ፤ ሰንበትን ለእኛ ዕረፍት ይሆን ዘንድ ሠራልን ደስታና ሰላም ለምናምን ሁሉ» እያልን በማለዳ ማመስገናችንም ከዚህ የመነጨ ነው፡፡ በባሕርይው ድካም የሌለበትና ዕረፍት የማይሻው አምላክ «ሰባተኛውን ቀን ባረከው፤ ቀደሰውም፤ ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ ዐርፎአልና» ተብሎ የተነገረው ከትንቢታዊ ትርጓሜው ባሻገር ሰንበት እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ዕረፍት እንደሚያስፈልገው አውቆ ያዘጋጃት ማረፊያ መሆኗንና በተግባር «ዐረፈ» መባልን ፈጽሞ መስጠቱን ያስረዳል፡፡ ከሰውም አልፎ የምትታረስ መሬት እንኳን ዕረፍት እንድታደርግ ማዘዙም ለፍጥረቱ ዕረፍት የሚያስብ አምላክ ያሰኘዋል፡፡ እንግዲያስ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ቀርቶላቸዋል፡፡ ወደ ዕረፍቱ የገባ እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ እርሱ ደግሞ ከሥራው ዐርፎአልና /ዕብ. 4.9/፡፡