አገልግሎቴን አከብራለሁ!

ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁም መንፈሳዊ ተቋማትን ለመገንባት ከሚቻልባቸው መሠረታዊ ተግባራቶች የምሕንድስና ሙያ ቀደምት ተጠቃሽ እንደመሆኑ በሀገራችን እንዲሁም በውጭ ሀገር ለሚገኙት የቤተ ክርስቲያናትና አድባራት ግንባትና መልሶ ማቋቋም ሥራ መሐንዲሶች እጅጉን ተፈላጊዎች ናቸው፡፡ በተለይም በሀገራችን ውስጥ ያሉ ቤተ ክርስቲያናት በጠላቶች ሥውር ደባና ጥቃት፣ ምዝበራ፣ ቃጠሎ እንዲሁም መራቆት የደረሳበቸው በመሆኑ እነዚህን ቤተ ክርስቲያናት መልሶ ለመንባትና አዳዲሶችን ለማነጽ በታቀደው ሥራ መሠረት የማኅበረ ቅዱሳን የምሕንድስና ባለሙያዎች ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል፡፡

የኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂን በማበልጸግም ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውሉ በርካታ ድረ ገጾችን አዘጋጅቶ በማቅረብ ለስብከተ ወንጌል ተደራሽነትና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ጥንካሬ ለመጨመር ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው፡፡ በመደበኛና በኢ-መደበኛ ዳታቤዝና ሲስተም ዴቨሎፕመንት ባለሙያ በሆኑ አገልጋዮች በመታገዝ ከተካተቱት ዋና ተግባራት በጥቅል ሲገለጽ የኮምፒዩተር ሲስተም እና የመረጃ ቋት ፍሎጎቶች ላይ ተስማሚ ቴክኖሎጂ በመጠቆም፣ በማበልጸግ እና ለብልሽቶች እንዲሁም ለጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ይሰጣል፡፡

ማኅበራዊ አገልግሎትን በተመለከተ ለምእመናን በልዩ ልዩ መንገዶች ግንዛቤ በመስጠት የማኅበራዊ አገልግሎት ተሳትፏቸውን ያሳድጋል:: ኦርቶዶክሳዊያን በማኅበራዊ አገልግሎት ያላቸው ተሳትፎ እንዲያድግ ስልት ቀይሶ ይተገብራል፤ የከፍተኛ ትምህረት ተቋማት ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች በማኅበራዊ፣ በሥራ ፈጠራና በኢኮኖሚ ተጽእኖ ፈጣሪ የሚሆኑበትን ትምህርት ክፍል እንዲመርጡ የተለያዩ ግንዛቤ እና ሥልጠና ይሰጣል::

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን ሁሉ መሰብሰቢያችን በመሆኗ ቅድስት ቤታችንን ልናንጽና ልንጠብቅ እንደሚገባ ቅዱስ ቃሉ እንዲህ ሲል አስተምሮናል፡ ‹‹ቤቴንም ሥሩ፡፡›› የእግዚአብሔር ቤት ቅድስናው ተጠብቆና ሥርዓቱ ሳይፋለስ ለሕዝበ ክርስቲያኑ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት ቅድስት ቤቱን በአምሳለ ግብሩ ተምሳሌት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን እናንጻለን፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንን የመገንባት ወይም የማስገንባት ሥራን የማካነወን ተልእኮ ማኅበረ ቅዱሳን ሥራዬ ብሎ የያዘው ተግዳሮት ነው፡፡ ማኅበሩ ለምእመናንና ለአብያተ ክርስቲያናት የሙያ አገልግሎት እንዲሰጥ ዕቅድና ስትራቴጂ በማውጣት በተለይም በገጠር ያሉ አብያተ ቤተ ክርስቲያናትንና ሕንጻ ግንባት ያንጻል፤ ያሳንጻል፡፡ (ሐጌ.፩፥፰)

‹‹እግዚአብሔር ፍቅር ነው›› (፩ኛ ዮሐ.፫፥፱)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ አጋማሽ ፈተናስ እንዴት ነበር? መቼም በርትቶ ሲማርና ሲያጠና ለነበረ ተማሪ ፈተናው እንደሚቀለው ተስፋ አለን፤ ጎበዝ ተማሪ የሚያጠናው ፈተና ሲደርስ ብቻ አይደለምና! መምህራን ሲያስተምሩ ተግቶ በአግባቡ የሚከታተል ያልገባውን የሚጠይቅ፣ መጻሕፍትን የሚያነብ የበለጠ ዕውቀት ለማግኘት ተግቶ የሚያጠና ነው!

ታዲያ እንደዚህ አድርጎ ትምህርቱን የሚከታተል ጥሩ ውጤትን ያመጣል! እንግዲህ በተለያየ ምክንያት በግማሽ ዓመቱ ፈተና በደንብ ያልሠራችሁ በቀሪው የትምህርት ዘመን በርትታችሁ በማጥናት ዕውቀትን እንድታገኙና ጥሩ ውጤት እንድታመጡ አደራ እንላለን!

ልጆች! ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁም ጎበዞች መሆን አለባችሁ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ተማሩ! መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ‹‹ተስፋ››  በሚል ርእስ  ስለ ተስፋ ተምረናል፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ፍቅር እንማራለን!

ጋብቻና ጾታ

የክርስቲያናዊ ጋብቻ መነሻውም መድረሻውም እግዚአብሔር ነው፡፡ በቅዱስ ጋብቻ ሁለቱ ወንድና ሴት በቅዱስ ቊርባን አንድ ይሆናሉ፡፡ መንግሥቱን ከሚያወርሰን ጋር ኪዳን ሳንገባ ጋብቻን ብንጀምር እንደ ብሉይ ኪዳን ዓለማዊ፣ ምድራዊ፣ ሥጋዊ ልጅ ለመውለድ፣ የፍትወት ፈቃድን ለመፈጸም ወይም ለመረዳዳት ብቻ ዓለማውን ያደረገ ይሆናል፡፡ በክርስቲያናዊ ጋብቻ ግን እነዚህ ራሱ እግዚአብሔር የሚሰጠን ስጦታዎች ሲሆኑ በእምነታችን ጸንተን በበጐ ምግባር ከኖርን ደግሞ ሰማያዊ መንግሥቱን እንወርሳለን፡፡

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

ማኅበሩ መንፈሳዊ አገልግሎት ተደራሽ ከማድረጉም በላይ አዳዲሲ አማንያኑ እንዲሁም ምእመኑ በሃይማኖት ጸንተው እንዲኖሩ ለማስቻል የተለያዩ መርሐ ግብራትንና ሥልጠና በማዘጋጀትና ተሳትፎአቸውን በመጨመር ያግዛቸዋል፡፡ በርካታ ኢ-መደበኛ አባላትንም በዚሁ የተነሣ ማፍራት በመቻሉ አገልግሎቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጨምሯል፡፡

ጋብቻና ጾታ

ፈቃድ ለሐሳብ መነሻ ነው፤ አንድ ሰው አንድን ጉዳይ ማሰብ የሚጀምረው ከፈቃዱ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ሐሳብና ፈቃድ በአገባባዊ ፍቺአቸው ተለዋዋጭና ተመሳሳይ የሚተካካ ትርጒም ይኖራቸዋል፡፡ ጋብቻም በጥሬ ትርጉሙ ኪዳን ማለት በመሆኑ በሁለት አካላት መካከል የሚፈጸም ውል ስምምነት ነው፡፡ አንድን ጎጆ ለመምራት በፈቃድ ላይ የሚመሠረት ውል (ኪዳን) ነውና፤ የጋብቻ ኪዳን በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን መጨረሻው ደግሞ ይህ ዓለም ሳይሆን ተስፋ የምናደርጋት መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርተ ወንጌልን በቃሉ አስተምሮ እንዲሁም ለሐዋርያት ቃሉን በዓለም እንዲዘሩ ‹‹ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ለፍጥረትም ሁሉ ወንጌልን ስበኩ›› ብሎ ባዘዛቸው መሠረት ወንጌል በምንኖርባት ምድር ለዘመናት ስትሰበክ ኖራለች፡፡ (ማር.፲፮፥፲፭) ጻድቃን አባቶቻችንም ለእኛ ሐዲስ ኪዳን ሰዎች ቃሉን በአደራ እንዳስረከቡንም በተመሳሳይ መልኩ ለልጆቻችንና ለልጅ ልጆቻችን የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረን በሃይማኖትና በክርስቲያናዊ ምግባር ኮትኩተን ማሳደግ ኃላፊነችን ነው፡፡

ማኅበራዊ ሕይወታችን!

ተወዳጆች ሆይ! ስሙ እንደ መዓር በሚጣፍጥ፣ መድኃኒትም በሚሆን፣ በቅዱስነቱ ዘለዓለም ያለ ረዓድ በአስጨናቂዎቻችን ፊት ክብር እና ሞገስ አግኝተን፣ ሕያውም ሆነን በምንኖርበት በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዴት ሰነበታችሁ? ፍቁራን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ፈቃድ፣ በባሕርይ አባቱ በአብ፣ በባሕርይ ሕይወቱ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስም ፈቃድ ሳምንቱን አልፈን በቀጣይ ክፍል እነሆ ተገናኘን!

በባለፈው ሳምንት ስለ ማኅበራዊ ሕይወታችን፣ በእኛ ዘመን ምን እየሆነ፣ ምን እየሠራን እያለፍን እንደሆነ፣ ካለፈው ዘመን ጋር እያመሳሰልን ከራሳችን ጋር እየመዘንን በስሱም ቢሆን ገረፍ አድርገን ለማየት ሞክረናል። ዛሬም ያንኑ ርእሰ አንቀጽ ይዘን ማኅበራዊ ሕይወት በክርስትና አስተምህሮ እና በዘለዓለማዊ የሕይወት ሽግግራችን ያለውን ምልከታ፣ የማኅበራዊ ሕይወት መሳሳት መንሥኤዎችን እና መዳኛ የሚሆነንን ጠቅሰን እናልፋለን።

ማኅበራዊ ሕይወታችን!

ሕይወታችንን ስናስብ የሌሎችን በሕይወት መቆየት እንጠባበቃለን። በጋራ ዓለም ላይ አብሮ የጋራ ዓለምን ማቅናት ላይ እንድንመረኮዝ እንገደዳለን። በሕገ ተፈጥሮ ውስጥ ለራሱ የተፈጠረ ፍጥረት የለም። ከእሑድ እስከ ዓርብ ያሉ ፍጥረታት እርስ በራሳቸው ተመጋጋቢ ቢሆኑም ሁሉም ግን ስለ አዳም ተፈጥረዋል። አንዳንዶቹ ለምግበ ሥጋ ምግበ ነፍስ፣ አንዳንዶቹ ለአንክሮ ለተዘክሮ፣ አንዳንዶቹ ለመድኃኒትነት፣ አንዳንዶቹ ለምስጋና፣ አንዳንዶቹ አዳም መሥዋዕት አድርጎ ሊያቀርባቸው፣ ሌሎቹ ደግሞ ለሌላ ለተለያየ ነገር ተፈጥረዋል። እነዚህ ሁሉ ለራሳቸው ሲባል አልተፈጠሩም።

የተራበችው ነፍሴ!

ቀንና ሌት ዙሪያዬን ከቦ ሲያስጨንቀኝ፣ ሲያሠቃየኝ የኖረው ባዕድ ከእኔ ባልሆነ መንፈስ ሊገዛኝና ከበታቹ ሊያደርገኝ ሲጥር በዘመኔ ኖሯል፡፡ ሥቃይና ውጥረት በተቀላቀለበት መከራ ውስጥ ብኖርም ሁል ጊዜ ተስፋን ማድረግ አላቆምኩም፤ ሆኖም ተፈጥሮዬ የሆነውን ሰላም ስናፍቅ የሰማይን ያህል ራቀብኝ፡፡