ሰማያዊ ቤት

መዓልት ለሌሊት ጊዜውን ሰጥቶ ሊያስረክብ ከግምሽ በታች ደቂቃዎች ቀርተውታል፤ ጠዋት ለስላሳ ሙቀቷን ከብርሃን ጋር፣ ከሰዓት ጠንከር ያለ ሙቀቷን ለምድርና ለነዋሪዎቿ እየሰጠች ወደ ምዕራብ ስትጓዝ የነበረች ፀሐይ ከአድማሱ ጥግ ግማሽ አካሏን ደብቃለች፡፡ ጠዋት ስትወጣ እየጓጓ ከሰዓት በማቃጠሏ ተማረውባት የነበሩትን ሰርክ በመጥለቋ እንዲናፍቋት ደብዛዛ ብርሃኗን እያሳየች ስንብቷን ጀምራለች!

የእምነት አርበኞች!

ሕዝቡን እያሳተ ከገደል ቢመራ

ትእዛዙ ሲፈጸም ለሥጋው የፈራ

የእምነት አርበኖች ሠለስቱ ሕፃናት

ከፊቱ በመቆም መሰከሩ ለእምነት

በእሳት ሲያስፈራ በሚከስመው ነዶ

ጣኦትን ሊያስመልክ ፈጣሪን አስክዶ

ከላይ ከሰማያት መልአክን አውርዶ

እሳቱ ሲበርድ ሰይጣን በዚህ ሲያፍር

ጽናት ተጋድሏቸው ገሀድ ሲመሰክር

የጽድቅ ብርሃን

በብርሃናት ልብስ ተሸልሞ…
በብዙ ሀብታት ያጌጠ
ሥጋን ከነምኞቱ ሰቅሎ…
ለምትበልጠው ጸጋ ያለመታከት የሮጠ

ይህ ነው ዜና ማርቆስ ትውልድ የሚያወሳው
የጽድቅ ብርሃን… ጧፍ ሆኖ የሚያበራው!

ጽዮን ሆይ ክበቢኝ!

የገባልሽ ኪዳን የሰጠሽ መሐላ

ከንቱ ነበረ ወይ የጨረቃ ጥላ?

በአጋንንት ፍላጻ ነፍሴ ብትወጋ

ምልጃሽ ነው ተስፋዬ ከጥላሽ ልጠጋ፡፡

ጽዮን ሆይ ክበቢኝ ለውዳሴሽ ልትጋ

የኃጢአት ጎዳናዬ መንገዴ ይዘጋ!

እኔም ልመለስ!

እኔም ልመለስ ድንግል እናቴ
ከስደት ሕይወት ከባርነቴ
በልጅሽ ጉንጮች በወረደ ዕንባ
ባዘነው ልብሽ በተላበሰው የኀዘን ካባ
በእናት አንጀትሽ እንስፍስፍ ብሎ ያኔ በባባ

ልመለስ ድንግል ሆይ እኔም ከስደት
እውነትን ልያዝ ልራቅ ከሐሰት፡፡

ጥላቻ ገዝቶኝ ወንድሜን ከጠላው
እምነት ምግባሬን ሰይጣን ዘረፈው
መልሽኝ ድንግል ይብቃኝ ግዞቱ
በምግባር እጦት በቁም መሞቱ!

ከውድቀት አነሣን!

ለሰሚው በሚከብድ ቃላት በማይገልጸው

በመከራ ውሎ አዳምን አዳነው!

ዲያብሎስ ታሠረ አዳም ነጻ ወጥቶ

ልጅ ተባለ ዳግም በደሉ ተረስቶ

የማይሞተው አምላክ ስለ እኛ ሲል ሞቶ

ከውድቀት አነሣን ልጅነትን ሰጥቶ!

የዛፉ ፍሬ

አዳም ያየ መስሎት ዓይኑ እንደተዘጋ
ይኖር ነበር ገነት ብቻውን ሲተጋ

ሔዋን ባትቀጥፈው የበለሱን ፍሬ
መቼ ይሰማ ነበር የአምላክ ልጅ ወሬ

አዳም የተከለው የፍቅር አበባ አድሮ እየጐመራ
አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን አብቦ ቢያፈራ
ከላይ ከሰማያት መንበረ ጸባኦት
የአምላክን አንድ ልጅ መዓዛው ጐትቶት

ወዮልኝ!

በኃጢአት ተፀንሼ በዐመፃ ተወልጄ
ከቃልህ ሕግ ወጥቼ በዝንጉዎች ምክር ሄጄ
በኃጢአተኞች መንገድ ቆሜ በዋዘኞች ወንበር ተቀምጬ
በውኃ ማዕበል ሰጥሜ የሞት ጽዋን ጨልጬ

የተራበችው ነፍሴ!

ቀንና ሌት ዙሪያዬን ከቦ ሲያስጨንቀኝ፣ ሲያሠቃየኝ የኖረው ባዕድ ከእኔ ባልሆነ መንፈስ ሊገዛኝና ከበታቹ ሊያደርገኝ ሲጥር በዘመኔ ኖሯል፡፡ ሥቃይና ውጥረት በተቀላቀለበት መከራ ውስጥ ብኖርም ሁል ጊዜ ተስፋን ማድረግ አላቆምኩም፤ ሆኖም ተፈጥሮዬ የሆነውን ሰላም ስናፍቅ የሰማይን ያህል ራቀብኝ፡፡

የከርቤ ኮረብታ

ከሕያው የመዐዘኑ ራስ ድንጋይ

ታንፆ በጽኑዕ ዐለት ላይ

ተዋጅታ በበጉ ደም ቤዛ

ሺህ ዓመታት ሺህ አቀበት ተጉዛ