በበረት ውስጥ እነሆ ተወለደ!

በመዝሙርና ሥነ ጥበባት ክፍል

ታኅሣሥ ፳፰፤፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

 

      ያቺ ድንግል ቤተ መቅደስ ሆና ሐርና ወርቅ ስታስማማ፣

መልአኩ የምትወልጅው ኢየሱስ ነው ያላትን ቃል ሳታቅማማ፣

የሚፈውስ ድውያንን፣

የሚያበራ ዕውራንን ፣

የሚተረትር ሽባዎችን ፣

የሚያነጻ ለምጻሞችን ፣

 የሚያወጣ አጋንንትን፣

ከስም በላይ ስም የሆነ፣

አልፋ ኦሜጋ የታመነ፣

ድንቅ መካር ሰው መሆንን የወደደ፣

በበረት ውስጥ እነሆ አሁን ተወለደ!

በአርያም የሚኖሩት መላእክቱ፣ ተመልክተው አምላክ ሲያዝን ለፍጥረቱ፣

ግርግም ከበው የዚያ ሕፃን ሠራዊቱ፣

በሰማያት አመስግነው እግዚአብሔርን

በምድር ላይ ለሰውም ልጅ ሰላም ይሁን

ብለው ዘምረው፣ ቤተ ልሔም የምድር ዙፋን፣

በአርያም ተሸክመው ቅዱስ አንተ የሚሉትን፣

ድንግል ማርያም ወዮሴፍ ላም አህያ ተመስለው አርባዕቱን፣

እነርሱ አንቺን ተሸክመው አንቺ ድገሞ ጸባኦትን

የአስተርእዮ ዘመን ሆኖ በምድር ላይ ሲከናወን

የሰማዩ ድንቅ ሥራ፣ ከበረት ውስጥ ሲፈነጥቅ ድህነት ፈውስን

ያነገበ የጽድቅ ጮራን፣

አንቺ ቅድስት ቤተ ልሔም፣

ቅጠል ለብሶ እንደ ሕፃን እያነባ መድኃኔ ዓለም፣

ኃያል ንጉሥ እርቃን ሆኖ ባንቺ ሲድር አልፈራሽም

እንደ ባሕር አልሸሸሽም

እንደ እምቦሳም አልዘለልሽም፡፡

እነ ኪሩብ በነደ እሳት የተሠሩ፣

በሁለት ክንፍ በዓለም ዙሪያ የሚበሩ፣

በመለኮት እሳትነት እንዳይጠፉ በሁለት ክንፍ ፊታቸውን የሠወሩ፣

በቀራቸው በሁለቱ እግራቸውን የጠፈሩ፣

 

  • ቅዱስ (፫)  ብለው ያለፋታ በመንቀጥቀጥ የሚያመልኩት፣

በግርግም ውስጥ እንደ ሕፃን ሲያለቅስ አይተው ምንስ አሉት

ፀሐይና ከዋክብትን ለፈጠረ፣

በልዩ ጌጥ ዓለማትን ላሳመረ፣

ነገሥተ ተርሴስ ወደሴያት፣

እጅ መንሻ አመሃውን ላመጡለት፣

ከዋክብትን በስማቸው ለሚጠራ፣

ፍጥረታትን ያለሳንካ ለሚሠራ፣

ከክብር አንሶ በራፊ ጨርቅ ተጠቅልሎ፣

አምላክ ሳለ ፍጡር መስሎ እንደ ነዳይ ተጎሳቁሎ፣

የዚያ ሌሊት ቢያይል ቁሩ፣

በደመ ነፍስ የሚኖሩ  ትንፋሽ ሰጥተው ሲገብሩ፣

መላእክቱ ቅዱስ(፫) ብለው በፍቅር ሆነው

የሚያመልኩት፣ በግርግም ውስጥ እንደ ሕፃን ሲያለቅስ አይተው

ምንስ አሉት ጽድቃችንም የመርገም ጨርቅ ከንቱ ሆኖ፣

መኖሪያችን በሲኦል ቋት ተወስኖ፣

ለዘመናት ስንገረፍ በእሳት ላንቃ፣

ያበቃ ዘንድ ይህ እንግልት ይህ ሰቆቃ፣

ልዑል ሁይ ክንድህን ስደድ፣

ናማ ውረድ

ና ተወለድ

ብለው ጻድቃን ሲጸልዩ ለዘመናት ፣

እርግማኑን ይሽረው ዘንድ በምርቃት፣

እነሆ አሁን

ጨለማውን አስወግዶ ብርሃኑን ያበራልን፣

ከጎሞራ ያልመሰለን ከሶዶም ግብር ያልደመረን፣

ሰማያትን በደመና የሚጋርድ፣

ተወለደ በዐውድ

እሰይ እሰይ ይኸው አሁን የምሥራች፣

የጸብ ግርዶሽ ተቀዳዶ ሰላም ሆኗል በላ በታች፡፡

፶፻፭፻ የንስሐ የጣር ዘመን ተፈጸመ

አምላክ ወሰብእ በግርግም ውስጥ ከበጎች ጋር ከተመ!

 

 

 

አዘክሪ ድንግል አዘክሪ!

ኀዳር ፭፤፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

አዘክሪ ድንግል አዘክሪ
ለልጅሽ አሳስቢ አዘክሪ

ለኃጥአን ለምኝልን
አይደለም ለጻድቃን

ከጠላት ሸሽተሽ ለተሰደድሽበት
በግብጽ በረኀ በሙቀቱ ውዕያት
በዱር በገደሉ በቁር ግሽበት

በጀርባዎችሽ አዝለሽ ለተጓዝሽበት
በመታቸው ተረከዞች እንቅፋት
ያን ሁሉ መከራ ለተቀበልሽበት

ለማዳን ሰውን ከጽኑ ግርፋት
ከሲኦል ትላትል ቁንጥጫ ከገሃነመ እሳት
ለአዳም ዘር በሙሉ የነፍስ ድኅነት
ለምኝልን እናት አትተይን በእውነት

አዘክሪ ድንግል አዘክሪ
ለልጅሽ አሳስቢ አዘክሪ!

የማይሞተው ሞተ!

በመዝሙርና ሥነ ጥበባት ክፍል

ጥቅምት ፳፮፤፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

ልዑል ሆይ ክንድህን ስደድ

ናማ ውረድ

ና ተወለድ

ብለው ነቢያት በጾም ጸሎት ተጉ ጮኹ!

ጨለማውን አስወግዶ ብርሃኑን ያበራልን

አንጠፋ ዘንድ በፍጹም ፍቅር የራራልን

 

በግብዞች በአይሁድ ሥርዓት

በሕጋቸው እንደጻፉት

የሾህ አክሊል ተቀዳጅቶ

መጻጻውን ተጎንጭቶ

 …..

እርሱ ሞተ ሊሰጥ ሕይወት

ወየው በሉ አልቅሱለት፤

የእጁን መዳን ያገኛችሁ የጌንሴሬጥ ድውይ ሁሉ

ለኢየሱስ አልቅሱለት፤ ፍዳን ስላያት በመስቀሉ

የ፲፪ ዘመን ሥቃይ በልብሱ ጫፍ ………

በቅጽበት ውስጥ የጠፋልሽ

ተገረፈ፤ ተንገላታ፤ የማይሞተው ሞትን ሞተ፤ ……..

ያ ርኅሩኅ ቸር መዳኒትሽ

ኢያሮስ የት ነው ያለህ!

ያ’ዓለም ጌታ ተተፋበት ሴት ልጅህን ያዳነልህ!

እመቤቴ የልጅሽን መከራውን እንዴት ቻልሽው አልልሽም

ቅዱስ ዳዊት በእሳት ፈረስ ሰባቱ ኃያል …..

መላእክቱ ካንቺ መጥተው ቢያፅናኑሽም

ለሦስት ቀን የአንዱ ልጅሽ ከሞቱ ይልቅ አሟሟቱ ….

እያስነባሽ እህል ውኃ እንኳን አልቀመስሽም

አብ ሆይ ማረን!

መንፈስ ቅዱስ ተዘከረን!

በልጅህ ደም የተገዛን ለመሆኑ አላወቅንም ዋጋችንን

ጽድቃችንም የመርገም ጨርቅ ከንቱ ሆኖ

መኖሪያችን በሲኦል ቋት ተወስኖ

ለዘመናት ስንገረፍ በእሳት ላንቃ

ያበቃ ዘንድ ይህ እንግልት ይህ ሰቆቃ

እሰይ እሰይ ይኸው አሁን የምሥራች

የሞት ዐዋጅ ተሻረልን፤ ገነት ዳግም ተከፈተች

የጥሉ ግድግዳ ፍርሶ ሰላም ሆኗል ከላይም ከታች

፶፻፭፻ የንስሐ የጣር ዘመን ተፈፀመ

በደላችን ተሰርዞ በክርስቶስ ደም ታተመ::

 

በእንተ ስምዐ ለማርያም

ዛሬ በፍልሰታዋ በአዛኝት የጾም ወራት

ልመናዬ አይደለም ፍርፋሪ ኩርማን ዱቄት

በደብረ ታቦሩ በዓል በተገለጸበት ምሥጢር

የዕለት ጉርሴን አልጠይቅም ቆሜ በደጅዎ በር

ልለምን . . . በእንተ ስማ ለማርያም

ስለ ወላዲተ አምላክ . . .

ተጠያቂው ማነው?

መምሬ እውነቱ ከንስሓ ልጆቻቸው ጋር በመሆን ሕሙማንን ለመጠየቅ በያዙት መርሐ ግብር መሠረት ከምእመናኑ ተወካዮች እና ከማኅበረ ካህናቱ ተወካዮች ጋር የተቃጠሩበት ሰዓት እስኪደርስ ከግቢያቸው ካለው ዛፍ ሥር ተቀምጠው ሌሎቹን በመጠበቅ ላይ ናቸው፡፡

ስማችን!

ሕፃን ሆኖ አባቷ፣ አባት ሲሆን ልጇ

በእምነት ያበረታት ወርዶ ከእቅፍ እጇ

ወደ ሞት እንዳትሄድ ሥቃይን ተሰቅቃ

ለልጄ እንዳትል የመከራ እሳት ሞቃ

ቆሞ መሰከረ ድምጹን አሰምቶ

ከአላዊው ንጉሥ በመንፈስ ተሞልቶ

ሰማያዊ ቤት

መዓልት ለሌሊት ጊዜውን ሰጥቶ ሊያስረክብ ከግምሽ በታች ደቂቃዎች ቀርተውታል፤ ጠዋት ለስላሳ ሙቀቷን ከብርሃን ጋር፣ ከሰዓት ጠንከር ያለ ሙቀቷን ለምድርና ለነዋሪዎቿ እየሰጠች ወደ ምዕራብ ስትጓዝ የነበረች ፀሐይ ከአድማሱ ጥግ ግማሽ አካሏን ደብቃለች፡፡ ጠዋት ስትወጣ እየጓጓ ከሰዓት በማቃጠሏ ተማረውባት የነበሩትን ሰርክ በመጥለቋ እንዲናፍቋት ደብዛዛ ብርሃኗን እያሳየች ስንብቷን ጀምራለች!

የእምነት አርበኞች!

ሕዝቡን እያሳተ ከገደል ቢመራ

ትእዛዙ ሲፈጸም ለሥጋው የፈራ

የእምነት አርበኖች ሠለስቱ ሕፃናት

ከፊቱ በመቆም መሰከሩ ለእምነት

በእሳት ሲያስፈራ በሚከስመው ነዶ

ጣኦትን ሊያስመልክ ፈጣሪን አስክዶ

ከላይ ከሰማያት መልአክን አውርዶ

እሳቱ ሲበርድ ሰይጣን በዚህ ሲያፍር

ጽናት ተጋድሏቸው ገሀድ ሲመሰክር

የጽድቅ ብርሃን

በብርሃናት ልብስ ተሸልሞ…
በብዙ ሀብታት ያጌጠ
ሥጋን ከነምኞቱ ሰቅሎ…
ለምትበልጠው ጸጋ ያለመታከት የሮጠ

ይህ ነው ዜና ማርቆስ ትውልድ የሚያወሳው
የጽድቅ ብርሃን… ጧፍ ሆኖ የሚያበራው!

ጽዮን ሆይ ክበቢኝ!

የገባልሽ ኪዳን የሰጠሽ መሐላ

ከንቱ ነበረ ወይ የጨረቃ ጥላ?

በአጋንንት ፍላጻ ነፍሴ ብትወጋ

ምልጃሽ ነው ተስፋዬ ከጥላሽ ልጠጋ፡፡

ጽዮን ሆይ ክበቢኝ ለውዳሴሽ ልትጋ

የኃጢአት ጎዳናዬ መንገዴ ይዘጋ!