ቅድስት አፎምያና ባሕራን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዐዋጅ ታውጀው ከሚጾሙ አጽዋማት አንዱ የሆነው ጾመ ሐዋርያት የሚጾምበት ወቅት ላይ ነንና ይህን ጾም እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችንን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን ከተቀበሉ በኋላ ወደ አገልግሎት ከመሄዳቸው በፊት ጾምን ጾመዋል፤ ይህን ጾም ምእመናን በየዓመቱ በዓለ ኀምሳ ከተከበረ ማግስት ጀምሮ እስከ ሐምሌ አምስት ቀን ድረስ እንጾመዋለን፤ ልጆች! እንግዲህ እኛም እንደ አቅማችን ይህንን ጾም መጾም ይገባናል፤ በዘመናዊ ትምህርታችሁም ከፈተና በፊት በርትታችሁ በማጥናት ፈተናውን በደንብ መሥራት ይገባችኋል ፤ መልካም! ለዛሬ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እንማራለን፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ቅዱሳን መላእክት ከእግዚአብሔር ተልከው እኛን የሚጠብቁን ናቸው፤ መልካም ስንሠራ ችግር በገጠመን ጊዜ በጸሎት ስንማጸናቸው ፈጥነው በመምጣት ከዚያ መከራ ያወጡናል፤ ከእግዚአብሔር አማልደው ምሕረትን ያሰጡናል፡፡ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ከመከራ ካዳናቸው መካከል ሁለቱን ታሪክ አንሥተን ለዛሬ እንማራለን፡፡

ጌታችን ፈዋሽ ውኃን አፈለቀ!

ሰኔ ስምንት ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው:: እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው::

ርደተ መንፈስ ቅዱስ

በዓለ ጰራቅሊጦስ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ፣ የቤተ ክርስቲያንን ልደትና የሐዋርያትን ለወንጌል አገልግሎት መታጠቅ የምናስብበት ታላቅና ቅዱስ በዓል ነው።

በዓለ ዕርገት

የበዓለ ዕርገት ታሪካዊ አመጣጥ ከራሱ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ ጋር የተያያዘ ነው። ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያቱ ለአርባ ቀናት እየተገለጸ፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት አስተምሯቸዋል። (ግብረ ሐዋርያት ፩፥፫) እነዚህ አርባ ቀናት ሐዋርያት ትንሣኤውን እንዲያረጋግጡና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያውቁ ያደረገባቸው ጊዜያት ነበሩ።

በዓለ ደብረ ምጥማቅ

አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም በግንቦት ሃያ አንድ ቀን ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ።

ዝክረ ቅዱስ ያሬድ

ሊቁ ደራሲ በተለወደ በ፸፭ ዓመቱ በሰሜን ተራራ ውስጥ ደብረ ሐዊ ከሚባል ገዳም  ግንቦት ፲፩ ቀን የተሠወረ እንጂ የሞተ አይደለም፡፡ እርሱንና ሥራዎቹንም በየዓመቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትዘክራለች፡፡ የዝማሬና መዋሥዕት መምህራን የቅዱስ ያሬድን ጉባኤ ተክተው አሁንም ድረስ በማስተማር ላይ ናቸው፡፡

‹‹ኢያቄም እና ሐና ሰማይን ወለዱ›› ቅዱስ ያሬድ

በመንፈስ ቅዱስ ግብር አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደች፣ የፈጣሪ እናት፣ የአምላክ እናት ለመሆን የበቃች በመሆኗ ቅድስት ድንግል ማርያም በሰማይ ትመሰላለች። አምላኳን በክንዶቿ ለመታቀፍ፣ ጡቶቿን ለማጥባት፣ በጀርባዋ ለማዘል የበቃች እመቤት ናትና። ባለማለፍ ጸንተው የሚኖሩት ሰባቱ ሰማያት እንዴት ነው ለእመቤታችን ምሳሌ የሚሆኑት እንል? ይሆናል። ይህም እንዲህ ነው፤ ከሰባቱ ሰማያት አንዱ ጽርሐ አርያም ይባላል። ሰማዩም የቅድስት ሥላሴ የእሳት ዙፋን ያለበት ነው። ‹‹ኢያቄም እና ሐና ሰማይን ወለዱ›› ስንል ጽርሐ አርያምን ወለዱ ማለታችን ነው።

ዘለዓለማዊ ሰላም

ፍጹም ጤና፣ ዕረፍት፣ ዕርቅ፣ ፍቅር፣ አንድነት፣ ደኅንነት፣ ተድላ፣ ደስታ፣ ሰላምታ፣ የቡራኬ የምርቃት ቃል ሰው ሲገናኝ የሚለዋወጠው የመልካም ምኞት መግለጪያ የሆነው ሰላም ለሁሉ ነገር መሠረት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፷፮) ምንጩ ደግሞ እውነተኛ ዘለዓለማዊ ሰላምን የሚሰጥ የሰላም አምላክ ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ የሰላም አለቃ ነውና ‹‹…የዘለዓለም አባት የሰላም አለቃ…›› እንዲል፡፡ (ኢሳ.፱፥፮) እውነተኛ ሰላም የሚገኘው ከእርሱ ዘንድ መሆኑን እንዲህ በማለት ነግሮናል፤ ‹‹…ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም…፡፡›› (ዮሐ.፲፬፥፳፯)

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አደረሳችሁ!

በዓለ ኪዳነ ምሕረት

ሰአሊተ ምሕረት፣ አቁራሪተ መዓት፣ ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ማኅደረ መለኮት፣ ብፅዕት፣ ከፍጥረት ይልቅ የተመሰገነች፣ እመ ብዙሃን፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለፍጥረት ሁለ ድኅነት ይሆን ዘንድ ከተወደደ ልጇ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን የተከበረች ናት፡፡