በዓለ ዕርገት
የበዓለ ዕርገት ታሪካዊ አመጣጥ ከራሱ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ ጋር የተያያዘ ነው። ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያቱ ለአርባ ቀናት እየተገለጸ፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት አስተምሯቸዋል። (ግብረ ሐዋርያት ፩፥፫) እነዚህ አርባ ቀናት ሐዋርያት ትንሣኤውን እንዲያረጋግጡና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያውቁ ያደረገባቸው ጊዜያት ነበሩ።
የበዓለ ዕርገት ታሪካዊ አመጣጥ ከራሱ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ ጋር የተያያዘ ነው። ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያቱ ለአርባ ቀናት እየተገለጸ፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት አስተምሯቸዋል። (ግብረ ሐዋርያት ፩፥፫) እነዚህ አርባ ቀናት ሐዋርያት ትንሣኤውን እንዲያረጋግጡና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያውቁ ያደረገባቸው ጊዜያት ነበሩ።
አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም በግንቦት ሃያ አንድ ቀን ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ።
ሊቁ ደራሲ በተለወደ በ፸፭ ዓመቱ በሰሜን ተራራ ውስጥ ደብረ ሐዊ ከሚባል ገዳም ግንቦት ፲፩ ቀን የተሠወረ እንጂ የሞተ አይደለም፡፡ እርሱንና ሥራዎቹንም በየዓመቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትዘክራለች፡፡ የዝማሬና መዋሥዕት መምህራን የቅዱስ ያሬድን ጉባኤ ተክተው አሁንም ድረስ በማስተማር ላይ ናቸው፡፡
በመንፈስ ቅዱስ ግብር አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደች፣ የፈጣሪ እናት፣ የአምላክ እናት ለመሆን የበቃች በመሆኗ ቅድስት ድንግል ማርያም በሰማይ ትመሰላለች። አምላኳን በክንዶቿ ለመታቀፍ፣ ጡቶቿን ለማጥባት፣ በጀርባዋ ለማዘል የበቃች እመቤት ናትና። ባለማለፍ ጸንተው የሚኖሩት ሰባቱ ሰማያት እንዴት ነው ለእመቤታችን ምሳሌ የሚሆኑት እንል? ይሆናል። ይህም እንዲህ ነው፤ ከሰባቱ ሰማያት አንዱ ጽርሐ አርያም ይባላል። ሰማዩም የቅድስት ሥላሴ የእሳት ዙፋን ያለበት ነው። ‹‹ኢያቄም እና ሐና ሰማይን ወለዱ›› ስንል ጽርሐ አርያምን ወለዱ ማለታችን ነው።
ፍጹም ጤና፣ ዕረፍት፣ ዕርቅ፣ ፍቅር፣ አንድነት፣ ደኅንነት፣ ተድላ፣ ደስታ፣ ሰላምታ፣ የቡራኬ የምርቃት ቃል ሰው ሲገናኝ የሚለዋወጠው የመልካም ምኞት መግለጪያ የሆነው ሰላም ለሁሉ ነገር መሠረት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፷፮) ምንጩ ደግሞ እውነተኛ ዘለዓለማዊ ሰላምን የሚሰጥ የሰላም አምላክ ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ የሰላም አለቃ ነውና ‹‹…የዘለዓለም አባት የሰላም አለቃ…›› እንዲል፡፡ (ኢሳ.፱፥፮) እውነተኛ ሰላም የሚገኘው ከእርሱ ዘንድ መሆኑን እንዲህ በማለት ነግሮናል፤ ‹‹…ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም…፡፡›› (ዮሐ.፲፬፥፳፯)
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አደረሳችሁ!
ሰአሊተ ምሕረት፣ አቁራሪተ መዓት፣ ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ማኅደረ መለኮት፣ ብፅዕት፣ ከፍጥረት ይልቅ የተመሰገነች፣ እመ ብዙሃን፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለፍጥረት ሁለ ድኅነት ይሆን ዘንድ ከተወደደ ልጇ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን የተከበረች ናት፡፡
አብዛኛው ሰው ሲሞት ጻዕረ ሞት አለበት፤ ማቃሰት፣ ማጣጣር፣ የሞትን አስፈሪ ድምፅ መስማትም የተለመደ ነው፡፡ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን ይህ ሁሉ የለባትም፡፡ ቅዱስ ቶማስ ስለ አሟሟቷ ጠይቋት ነበር፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ ለመግለጽ አዳጋች ሆኖ እንጂ በርካታ ነገሮችን ነግራዋለች፡፡ እናም ‹‹የሞት ጻዕር እንዴት አመመሽ›› ይላታል፡፡ እርሷም ‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም፤ ነፍሴ ያለ ድካም /ሕማም/ በደስታ ተለየች….›› በማለት ያለ ሕማም ያለ ድካም፣ ያለ ጭንቅ ያለ ጻዕርና ጋር በደስታ ነፍሷን ከሥጋዋ እንደተለየች ነግራዋለች፡፡ (ድርሳነ ማርያም ገጽ ፻፴፩)
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ሙሽራ አጊጣ፣ ለበጉ ሰርግ ያለ እድፍና ያለ ነውር ውብ ሆና ተዘጋጅታ በምትቀርብበት በዚያ ሰማያዊ ሰርግ ለመገኘትና ወደ በጉ ሰርግ ራት ገብተን፣ ካጌጡ ቅዱሳን ጋር ለመቀመጥና ለመብላት የበቃን ያድርገን፡፡
ውድ ክርስቲያኖች! ይህ የሰው ልጅ ታሪክ የተቀየረበትን ዕለት በደስታ፣ በፍቅር፣ የተጣላን ታርቀን፣ የበደልን ክሰን፣ በኃጢአት ያደፈ ሕይወታችን በንስሐ አንጽተን፣ በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ሕይወታችንን አስቀድሰን እናክብረው!
መልካም በዓል!