“የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ” (ዮሐ.፪፥፲፮)
በቅዱስ ያሬድ ድጓ ውስጥ የምናገኘው ዐቢይ ጉዳይ አንጽሆ ቤተ መቅደስ ነው። “የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት” እንዲል። ይህ ብቻ አይደለም፤ ተቆጣቸው፤ ገሠጻቸው የሚሉ አስተማሪ ቃላቶችን አካቶ ይዟል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ይህንን በተመለከተ እንዲህ ይላል፡፡” በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።” (ዮሐ.፪፥፲፬-፲፮)