‹‹ስለማስመሰል ርኅራኄው ሰይጣንን ተጠንቀቀው›› ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

የሰይጣን የማስመሰል ርኅራኄው የቱን ያህል አሳሳች እንደሆነ እንኳን አንረዳውም፡፡ ካሳተን በኋላም ያሳተን እርሱ መሆኑን መረዳት እየተሳነን ለውድቀታችን ሰዎችን፣ ዕድልን፣ ሁኔታዎችን እና ጊዜን ሰበብ እንድናደርግ ያደርገናል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሚሆነው በተለይ በየጠበሉ ‹‹እከሊት ናት መድኃኒት ያደረገችብሽ፤ እከሌ ነው መድኃኒት ያደረገብህ›› እያለ ራሱን ሲያጋልጥ የምንሰማው የሰዎች ታሪክ እማኝ ነው፡፡ ‹‹ሐሰተኛ ነውና፤ የሐሰት አባትም ነው›› እንደተባለው፡፡ (ዮሐ. ፰፥፵፬) በዚህ ሐሰተኛነቱም አንዳንዶችን የአጋንንቱን ምስክርነት አምነው እንዲካሰሱ ባስ ሲል ወደከፋ ነገር እንዲደርሱ ያደርጋቸዋል፡፡

«አቤቱ፥ አምናላሁ፤ ነገር ግን አለማመኔን ርዳው» (ማር.፱፥፳፬)

«እምነትስ፣ ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የምታረጋግጥ፥ የማናየውንም ነገር የምታስረዳ ናት» (ዕብ. ፲፩፥፩) እንደተባለው ሰው ተስፋን ከአምነት ያገኛል፡፡ አዳም ቢበድልም እንኳን ቸሩ አምላክ እግዚአብሔር በኋላ ዘመን ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል በጋባለት ጊዜ ተስፋ አግኝቷል፡፡ የመዳኑን ነገር በእምነቱ ተስፋ ሆነለት፡፡ እምነት ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር የምንገልጥበት፣ እርሱን ደስ የምናሰኝበት የሕይወት መሠረት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ሲያስረዳ «ያለ እምነትም እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም» ብሏል፡፡ (ዕብ.፲፩፥፮)

‹‹የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ›› (ዮሐ.፪፥፲፮)

በዐቢይ ጾም ሦስተኛው ሳምንት በእለተ እሑድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ፤ በቤተ መቅደስም በሬዎችንና በጎችን፥ ርግቦችንም የሚሸጡትን፥ ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፡፡ ይህን ባለመውደዱም የገመድ ጅራፍ ካበጀ በኋላ በጎችንና በሮዎችን እንዲሁም ሁሉንም ከቤተ መቅደስ አስወጣቸው፤ የሻጮቹንም ገንዘብ በተነባቸው፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፤ ርግብ ይሸጡ የነበሩትን ደግሞ ‹‹ይህን ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ አላቸው፡፡›› (ዮሐ.፪፥፲፬-፲፮)

‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› (ዮሐ. ፲፥ ፲፮)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአንቀጸ አባግዕ ሲያስተምር ‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› ብሏል።(ዮሐ. ፲፥ ፲፮)

ጥምቀተ ክርስቶስ

በቅዱስ ዮሐንስ እጅ በማየ ዮርዳኖስ ተጠምቆ የባሕርይ ልጅነቱንና አምላክነቱን ከአብ እና ከመንፈሰ ቅዱስ አስመሰከረ፡፡

ዘመነ አስተርእዮ

አስተርእዮ መታየት ወይም መገለጥ የሚል ትርጓሜ ያለው የግእዝ ቃል ነው፡፡ በግሪክ ‹‹ኤጲፋኒ›› የሚል ስያሜ አለው፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትም ይህን ቃል በመጠቀም ኤጲፋኒያ እያሉ በዜማ መጻሕፍቶቻቸው ይጠሩታል፡፡

‹‹የገሃነም ደጆችም አይችሏትም›› (ማቴ.፲፮፥፲፰)

ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው ‹‹የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ÷ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ፡፡ እኔም እልሃለሁ÷ አንተ ጴጥሮስ ነህ፤ በዚያች ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ÷ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም፡፡››(ማቴ.፲፮፥፲፫—፳)

ጌታችን ኢየሱስ ተወለደ

ለአምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን በዓለም ላይ ሠልጥኖ የነበረውን ጨለማ ያስወግድ ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ሰው ሆነ፡፡ ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው አማናዊው ብርሃን ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ በሥጋ ተገለጠ፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴው እንዳለው ‹‹ብርሃን ዘበአማን ዘያበርህ ለኵሉ ሰብእ ለእለ ይነብሩ ውስተ ዓለም፤ በጨለማ ውስጥ ለሚኖር ሕዝብ ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው›› (ኢሳ. ፱፥፪)፡፡

ሐዲስ ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኢትዮጵያ

አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሚታወሱባቸው በዓላት መካከል ታኅሣሥ ፳፬ ቀን የሚከብረው በዓለ ልደታቸው አንደኛው ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ዜና ልደታቸውን ሲናገር ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› በማለት በክብር ጠርቷቸዋል፡፡

‹‹እጅህን ከአርያም ላክ፤ አድነኝም›› (መዝ. ፻፵፫፥፯)

በየዘመኑ የተነሡ ነቢያትም ምንም እንኳን አምላክ ይህን ዓለም እንዴት እንደሚያድነው በግልጽ ባይረዱትም እግዚአብሔር ዓለሙን የሚያድንበትን ቀን እንዲያቀርበው እንዲህ እያሉ ይማፀኑ ነበር፤ ‹‹አቤቱ ሰማዮችን ዝቅ ዝቅ አድርጋቸው፤ ውረድም፤ ተራሮችን ዳስሳቸው ይጢሱም፡፡ መብረቆችህን ብልጭ አድርጋቸው፤ በትናቸውም፤ ፍላጾችን ላካቸው፤ አስደንግጣቸውም፡፡ እጅህን ከአርያም ላክ፤ አድነኝም›› (መዝ. ፻፵፫፥፭-፯)፡፡