ወርኃ መጋቢት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ሰባተኛው ወር ወርኀ መጋቢት ይባላል። መጋቢት በቁሙ “ስመ ወርኅ፣ ሳብዕት እመስከረም፣ የመዓልትና የሌሊት ምግብና ትክክል የሚሆንበት ወርኅ ዕሪና” ማለት ነው። “እስመ ይዔሪ መዓልተ ወሌሊተ አመ እስራ ወኀሙሱ ለወርኀ መጋቢት፤ በመጋቢት ወር ፳፭ ቀን ሌሊቱና መዓልቱ ይስተካከላልና” እንዲል፡፡ (ዲድስቅልያ ፴፣ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፭፻፸፯)