የሥራ አጥነት ተጽዕኖ

ጥቅምት ፳፤፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

“በሕይወት ዘመንህም ሁሉ በድካም ከእርሷ ትበላለህ” የሚለው አምላካዊ ቃል ሁላችንንም የሚመለከት ነው፡፡ (ዘፍ. ፫፥፲፯) ሰው በሠራው ኃጢአትና ጥፋት የተነሣ ከገነት ተባሮ ወደ ምድር ከመጣበት ጊዜ አንሥቶ እስካለንበት ጊዜ ድረስ የሥጋችንን በተለይም መሠረታዊ ፍላጎታችንን ሟሟላት የምንችለው ሥራ ሠርተን በምናገኘው ገንዘብና ቁሳዊ ነገሮች ነው፡፡

በዘመናት ሂደት ሰዎች በተለያዩ ችግሮችና መከራዎች ውስጥ ገብተው የሚዋዥቁበት ምክንያት አንድም በሥራ አጥነት ሳቢያ በሚያጋጥም የገንዘብ አቅም ማነስና ችግር በመሆኑ የምግብ አቅርቦት፣ የመጠለያ እጦትና የአልባሳት እጥረት ለረኃብ፣ ለመራቆት እንዲሁም ለተለያዩ በሽታዎች ባስ ሲል ደግሞ ለሞት ይዳርጋሉ፡፡

የሥራ አጥነት ችግር አስከፊነት ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በደረስንበት በዚህ ወቅት በተለይም ወጣቶች ከዚህ ለባሳ ችግር ተጠቂ ሆነዋል፡፡ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸው እንዲሁም በተሰጣቸው ተሰጥኦ ለፍተው፣ ጥረው፣ ግረው የመኖር ሐሳባቸው ከማንኛውም የዕድሜ ክልል የበለጠ በመሆኑ አእምሮአቸው ሥራ ሲፈታ ይረበሻል፤ ተስፋም ያጣሉ፤ ወደ ጭንቀትና የተለያዩ የሥነ ልቡና ቀውስ የሚገቡ ወጣቶች ቁጥርም ጥቂት አይባልም፡፡

በየዓመቱ ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት በተለያዩ የትምህርት ዘርፍ ተመርቀው የወጡ ተማሪዎችም ሆነ በዘመናዊ ትምህርት ብዙ ሳይገፉ በአጋጣሚዎች ተጠቅመው በሙያቸው አልያም በጉልበታቸው ሠርተው ለመኖር የሚጥሩ ወጣቶች በልዩ ልዩ የሀገራችን ክፍሎች ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ግን ሥራ አግኝቶ በቋሚነት አንድ ቦታ ላይ ገንዘብም፣ ዕውቀትም ሆነ ልምድ ማካበት ያልቻሉ በርካቶች ናቸው፡፡ ይህም እራሳቸው ላይ ብቻ ሳይሆን ቤተ ሰቦቻቸው እንዲሁም ማኅበረሰቡ ላይ የሚያመጣው ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው፤ አብዛኞቻችን በእራሳችን፣ በዘመዶቻችንና በጎረቤቶቻችን ሕይወት የሰማነውና የተመለትነው ነገር ነው፡፡

በርካታ ወጣቶች የሱሰኝነት ተጠቂ የሆኑት በዚህ ምክንያት እንደሆነ ከገዛ አንደበታቸው ሰምተንም ሊሆን ይችላል፡፡ በተለይም ወጣት ወንዶች ለዚህ ችግር ተጋላጮች ናቸው፡፡ ሱሰኝነት የሚያመጣው የጤንነት እክል ብቻ እንዳልሆነ ደግሞ የጤና ባለሙያዎች አበክረው ይናገራሉ፡፡ እንደ እነርሱ ገለጻ ከሆነ ሱሰኞች ከቤተ ሰቦቻቸው ጋርም ሆነ ከማንኛውም የማኅበረሰብ አካል ጋር መልካም ግንኙነት አይኖራቸውም፡፡ የተዛበ ቀኖችን በማሳለፋቸው የተነሣ ከማንም ጋር የሰላም ግንኑነት ሊኖራቸው አይችልም፡፡ ቀኑ ለእነርሱ ሌሊት፣ ሌሊቱ ደግሞ ቀን የሚሆንባቸው ጊዜ ጥቂት አይደለም፡፡ ንግግራቸው በአብዛኛው ቀና ያልሆነና የተጣመመ እንዲሁም ስድብና አጸያፊ ቃል የተቀላቀለበት ሲሆን ከሰዎች ጋር የመጣላቱ ዕድል ሰፊ ይሆናል፡፡ የሚወዷቸውንና የሚቀርቧቸውን ሰዎች ሳይቀር ስለሚያስቀይሙ በብቸኝነት ዓለም ውስጥ ይገባሉ፡፡

ሱሰኛ የሚሆኑ ወጣቶች ዓለማዊ ሕይወትን የሚኖሩ ብቻ ሊመስለን ይችላል፡፡ ነገር ግን በስመ ኦርቶዶክስ የሚኖሩና በሥራ አጥነት እንዲሁም በሌሎች ተጓዳኝ ችግሮች ምክንያት ባክነው የቀሩ ብዙዎች እንዳሉ ማወቅ ይገባል፡፡

በዚህ ጊዜ ደግሞ የተጋፈጥነው ሌላ ትልቅ ችግር አለ፡፡ ከምዕራባውያን በኩል ወደ ሀገራችን የገባና የተስፋፋ ተብሎ የሚታመነው “የሰይጣን አማኞች ማኅበረሰብ” ወጣቶችን በገንዝብና ሌሎች ጥቅሞች በማጥመድ የጠላት መረብ ውስጥ እየከተቱ ይገኛሉ፡፡ በየአደባባይ እየተመለከትናቸው ያለነው የእምነቱ ተከታዮች ሳያውቁም ይሁን አውቀው ለሰይጣን እየተገዙ ነው፡፡ ድህነትን ሸሽተው፣ በቀላሉና በአጭር ጊዜ ችግራቸውን ፈትተው ገንዘብና ሀብት ለማካበት በሚደረግ ጥረት ነፍሳቸውን ካጡት ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን እንዳሉበት ተአማኒ ምንጮች ይናገራሉ፡፡ ወጣቶቹ ታዲያ እያጡ ያሉትን መንፈሳዊነትም ሆነ እየገቡበት ያለውን አዘቅት በደንብ የተረዱ አይመስሉም፡፡ ብቻ የዕለት ጉርሰን ለሟሟላትና ከተቻለም በርከት ያለ ገንዘብ ለማግኘት ወደዚህ ዝቅተት ይገባሉ፡፡ በኋላ ግን ከገቡበት ለመውጣት ቢፈለግ እንኳን ቀላል እንዳልሆነ መገመት አያዳግትም፡፡

ኢትዮጵያ ሀገራችን እያስተናገደች ያለችው አስተዳደራዊ ለውጥና ማኅበረሰባዊ አኗኗር ያመጣው የኑሮ ውድነትም ለዚህ ችግር ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደረገ ነው፡፡ ቢያንስ መሠረታዊ ነገሮች ሁሉም ሊኖረው ይገባልና በእራሱ ለፍቶ እንዲያገኝ የማድረግ ዕድል ተጠያቂው አካል ሊያመቻች ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም ይህን እንደምትደግፍ አስቀድመን በጠቀስነው የአምላካችን ትእዛዝ ማረጋገጥ እንችላለን፡፡

    ይቆየን!

የአበባ ወር

መስከረም ፳፮፤፳፻፲፰ ዓ.ም.

ጊዜ የተለያዩ ተፈጥራዊ ኩነቶችን ያስተናግዳል፤ በዓለም ላይ በሚከሰቱ የወቅቶች መፈራረቅም ምድር አንዳንዴ ስትበለጽግ ሌላ ጊዜ ደግሞ ትራቆታለች፡፡ በክረምት ወራት በሚዘንበው ዝናብ ስትረጥብ በበጋ ደግሞ በፀሐይና በሙቀቱ ትደርቃለች፡፡ በዘመነ መጸው በነፋሳት ስትናወጥ ፈክተው የሚያብቡት አበቦች ግን ያስውቧታል፡፡

ቅዱሱ ሰው አባ ጽጌ ድንግል የአበቦችን ዕጹብ ድንቅ ተፈጥሮና የላቀ ዋጋ በማወቁ ሳይሆን አይቀርም ከአበቦች ሁሉ በሚበልጥ አበባ ለምንመስላት ድንግል ማርያም አበቦችን ያበረከተላት፡፡ በዐሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሱት ሊቁ የደረሱት የማኅሌተ ጽጌ ድርሰት ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፭ ቀን ድረስ ባለው ወቅት የእመቤታችን ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ ብሎም ወደ ኢትዮጵያ መሰደድ እና መንከራተት እንዘክርበታለን፡፡

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት፣ አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤አሜን!

ደመራ

መስከረም ፲፬፤፳፻፲፰ ዓ.ም.

የታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እናት ንግሥት እሌኒ ከቁስጥንጥንያ ተነሥታ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል ከተቀበረበት ለማውጣት ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘች፡፡ በደረሰች ጊዜ የጌታችን መስቀል ተአምራትን እንዳያደርግ አይሁድ በምቀኝነት ቀብረውት ነበርና የተቀበረበትን ቦታ የሚያሳያት አጥታ በመፈለግ ብዙ ጊዜ አሳለፈች፡፡

ኪራኮስ የሚባለው አረጋዊ ሰው መስቀሉ የተቀበረበትን በሥቃይና በመከራ አስጨንቃ ስትይዘው እንደነገራት ታሪኩ ያስረዳናል፤ ቁፋሮ ልታደርግበት የምትችለውን አካባቢም ሲጠቁማት ደመራ አስደምራ ዕጣን አጢሳ ወደ ፈጣሪዋ ተማፀነች፡፡ የዕጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ ከወጣ በኋላ መንበረ ጸባዖት ደርሶ ተመልሶ መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ አመለከታት፡፡ ንግሥቷም በምልክቱ መሠረት ማስቆፈር ጀመረች፡፡ ለማስቆፈር የወሰደባት ጊዜም ከመስከረም ፲፯ እስከ መጋቢት ፲ ነበር፡፡ በቁፋሮውም መጨረሻ ሦስት መስቀሎችን አገኘች፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እነዚህ መስቀሎች አንዱ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክቡር መስቀል እንደሆነ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ፈያታዊው ዘየማንና ፈያታዊው ዘጸጋ ሁለቱ በጌታ ቀኝና ግራ የተሰቀሉት ወንበዴዎች እንደሆኑ ይገልጻሉ፡፡

ንግሥት እሌኒ ሦስቱን መስቀሎች ካገኘች የጌታችን መስቀል ለይታ ለማወቅ የሞተ ሰው አስከሬን አምጥታ በላያቸው ላይ አደረገቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ሙቱን አስነሣው፡፡ ይህን ጊዜ ለይታ ያወቀችውን መስቀል በክብር ወስዳ የቤተ ክርስቲያኑም መሠረት ወዲያው እንዲጣል አደረገች፤ የደመራ ሥርዓት ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚከበር ነው፡፡

ደመራ ማለት “መጨመር፣ መሰብሰብ መከመር” ነው፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌም የቃሉን ፍቺ  “ደመረ” ከሚለው የግእዝ ቃል አውጥተው ደመራ ግእዝና አማርኛን የአስተባበረ መሆኑን ይናገራሉ፤ አያይዘውም የበዓለ መስቀል ዋዜማ እንጨቶች የሚደመሩበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ (ሰዋሰወ ግእዝ ወግስ መዝገበ ቃላት) በየዓመቱ የመስቀልን በዓል ስናከብር ደመራ የምንደምረውና የምናበራው ቅድስት ዕሌኒን አብነት በማድረግ ነው፡፡

የበረከት በዓል ያድርግልን፤ አሜን!!!

 

ነገረ ጳጕሜን

ኢትዮጵያ የራሷ ባህል፣ ታሪክና ሃይማኖት ያላት ይህንም በትውፊትና በመጽሐፍ ቅዱስ ይዛ የቆየች ሀገር ናት፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው ውሸት ቢናገርና በውሸታሞች መካከል ቢደገፍ ሌሎችም ውሸት ይናገሩ እንደማይባል ኢትዮጵያም ሌሎች በንጉሣቸው በጣዖታቸው ስም በየጊዜው እየቀያየሩ የዘመን ቆጠራን ቢያከብሩ የራሷን እውነት ትታ የእነርሱን ውሸት ትቀበል እንደማይባል መረዳት ይጠይቃል።

ወርኃ ነሐሴ

ነሐሴ የሚለውን ቃል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ላይ “ናሴ” ማለት መጨረሻ የመስከረም ዐሥራ ሁለተኛ በማለት ይፈቱታል፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝመበ ቃላት ገጽ ፮፻፴፯)

የቱን ታስታውሳላችሁ?

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና ዕርገት መታሰቢያ ለሆነው ጾመ ፍልሰታ አደረሳችሁ፡፡ ልጆች! በየዓመቱ በጉጉት የምንጠብቃት ጾመ ፍልሰታን እንደ አቅማችን በመጾምና በመጸለይ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤዛዊተ ዓለም በረከትን መቀበል ይገባናል፤ ልጆች! በጾመ ፍልሰታ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ፣ ትምህርት በመማር፣ በማስቀደስ፣ መልካም ምግባራትን በመፈጸም መሳተፍ አለብን፡፡

ልጆች! በዛሬ “የቱን ታስታውሳላችሁ?” መርሐ ግብራችን ባሳለፍነው ዓመት ስንማራቸው ከነበሩ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባራት መካከል የተወሰነ ጥያቄን አዘጋጅተንላችኋል፡፡ ከዚህ ቀደም የአስተማርናችሁን ትምህርት በደንብ ከልሷቸው፤ ከዚያም ለጥያቄዎቹ ተገቢውን ምላሽ በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ! እንደተለመደው ጥሩ ውጤት ለሚያመጡ ልጆች ሽማቶችን አዘጋጅተናል፡፡

ተጠያቂው ማነው?

መምሬ እውነቱ ከንስሓ ልጆቻቸው ጋር በመሆን ሕሙማንን ለመጠየቅ በያዙት መርሐ ግብር መሠረት ከምእመናኑ ተወካዮች እና ከማኅበረ ካህናቱ ተወካዮች ጋር የተቃጠሩበት ሰዓት እስኪደርስ ከግቢያቸው ካለው ዛፍ ሥር ተቀምጠው ሌሎቹን በመጠበቅ ላይ ናቸው፡፡

‹‹አትጨነቁ…›› (ማቴ.፮፥፴፬)

ሰዎች  መልካምና ክፋ ነገርን ለማሳካት ይጨነቃሉ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹አትጨነቁ›› ያለን ለክፋትና ለኃላፊው ዓለም ተጨንቀን መፍትሔ ለማናመጣለት ነገር ነው፡፡ (ማቴ.፮፥፴፬) ፈጣሪያችን ለእኛ ለልጆቹ በዚህ ምድር በእንግድነት ስንኖር ምን እንደሚያስፈልገን ያውቃል፤ የሚያሻንንም ይሰጠናል፤ እናስብ ዘንድ አስተዋይ አእምሮ ሰጥቶናል፤ ማሰብ ከሚገባን በላይ ደግሞ ልንጨነቅ ስለማይገባ ‹‹አትጨነቁ›› አለ፡፡ አበው በብሂላቸው ‹‹…አስብ እንጂ አትጨነቅ..›› የሚሉን ለዚህ ነው፡፡ በምድር ስንኖር በማሰብ በመጠንቀቅ፣ በመጠበቅ እንደ ርግብ የዋህ እንደ እባብ ደግሞ ብልህ ሆነን ልንኖር ያስፈልጋል፡፡ ልንፈራና ልንጨነቅ እንደማይገባ ግን ክርስትናችን ያስተምረናል፡፡ ጌታችን ለአባቶቻችንን ቅዱሳን ሐዋርያት ስለሚቀበለው መከራ፣ ስለሞቱ ሲነግራቸው ባዘኑ ጊዜ ‹‹…ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም ደግሞ እመኑ…›› በማለት በአንዳች ነገር እንዳይጨነቁ ልባቸው እንዳይታወክ ነገራቸው፡፡ (ዮሐ. ፲፬፥፩)

የቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ካርታ

ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንደምንከረማችሁ? እንደምን ሰነበታችሁ? የዛሬ የዚህ ክፍለ ጽሑፍ ዓላማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የመጭው ዐሥር ዓመታት የመንፈሳዊ እና ዘላቂ ልማት ግቦችን ማስተዋወቅ ነው፡፡

የቤተ ክርስቲያንን የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በዝርዝር ከመዳሰሳችን በፊት ዕቅድ ምን እንደሆነና የዕቅድን አስፈላጊነት በትንሹ መዳሰስ አስፈላጊ ነው፡፡

“እግዚአብሔርን የምትወዱ ክፋትን ጥሉ” (መዝ.፺፯፥፲)

በባሕርይው ፍጹም፣ ቅዱስ፣ ንጹሕ የሆነና ምንም ዓይነት ርኩሰት የማይስማማው አምላካችን እግዚአብሔር መልካም አባት ነው፡፡ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድሞ የነበረ፣ አሁን ያለ ወደ ፊትም ዓለምን አሳልፎ የሚኖር በመሆኑም ለዘለዓለም በቅድስና ይኖራል፡፡ ፍጥረቱን በሙሉም በቸርነቱ ከመፍጠሩ በፊት ሲቀደስ ሲለስ ይኖር የነበረ፣ አሁንም በፍጥረቱ እንዲመሰገን፣ እንዲቀደስ፣ እንዲወደስ የፈቀደ፣ ወደፊት ደግሞ በክብር ምስጋና በመንግሥቱ ሊገዛ የሚወድ ፈጣሪያችን ክብሩንና ቅድስናውንም ለፍጥረቱ በተለይም ለቅዱሳን መላእክት እና ሰው የሚያደርግ ነው፡፡ ይህን ሁሉም በቸርነቱ፣ በመልካምነቱ፣ በበጎነቱ፣ ስለ ቅዱስ ፈቃዱ አድርጓል፡፡