ወርኃ ግንቦት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ዘጠነኛው ወር “ግንቦት” በመባል ይታወቃል፡፡ ግንቦት “ገነበ፣ ገነባ፣ ሠራ፣ ቆፈረ፣ ሰረሰረ” ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጒሙም “ገቦ፣ ክረምት፣ የክረምት ጎን፣ ጎረ ክረምት (የክረምት ጉረቤት)” ይባላል። ይህንም ስም የሰጡት የክረምት መግቢያ ምድር ለእርሻ የምትዘጋጅበት ወቅት በመሆኑ ነው።

አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል ሲተረጒሙ “ስመ ወርኅ፣ ታስዕ እመስከረም፣ ገቦ ክረምት፣ ጎረ ክረምት” ይልና በግንብ ዘይቤ ሲፈቱት ግን “ወርኀ ሡራሬ” ያሰኛል፡፡ የባቢሎን ግንብ ሳይቀር ሁለቱ መቅደሶች በግንቦት ወር ተመሥርተዋል፡፡ (፫ኛ ነገ.፮፥፩፣ ዕዝ.፫፥፰) ይሉታል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፫፻፳፪)

የሕይወት መዓዛ

መድኃኒዓለም ክርስቶስ ሕይወትን ያጣጣምንበትና ያሸተትንበት መልካም መዓዛ መሥዋዕት ነው!

ሰላም!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ዐቢይ ጾም (ጾመ ክርስቶስ) ጨርሰን በዓለ ትንሣኤን እያከበርን ነው፤ በዓሉን እንዴት እያከበራችሁ ነው? የትንሣኤ በዓል ነጻነታችንን አግኝተን ትንሣኤ እንዳለን የተበሠረበት በዓላችን ነውና ታላቅ በዓል ነው፡፡

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶ ሞትን ድል አድርጎ በመነሣቱ ትንሣኤያችንን አበሠረን፤ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለን ዐወቅን፡፡ ታዲያ በጾሙ ወቅት እናደርገው እንደነበረው በጸሎት መበርታትና በመንፈሳዊ አገልግሎት መሳተፍ አለብን፤

በዘመናዊ ትምህርታችን መበርታት እንዳለብንም መዘንጋት አይገባም፡፡ አሁን ያለንበት ጊዜ ትምህርቱ መገባደጃ ወቅት ስለሆነ ከፈተና በፊት በርትተን በማጥናት ዕውቀትን አግኝተን ከክፍል ክፍል በጥሩ ውጤት መሸጋገር ይገባናል፤ መልካም! ለዛሬ ከበዓለ ትንሣኤ ጋር በተያያዘ ስለ ሰላም እንማራለን፡፡

ወርኃ ሚያዝያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ስምንተኛው ወር  “ወርኃ ሚያዝያ” በመባል ይታወቃል፡፡ ሚያዝያ ማለት “መሐዘ፣  ጎለመሰ” ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን “ጎለመሰ፣ ጎበዘ፣ አደገ፣ ሚስት ፈለገ፣ የሚዜዎችና የሙሽሮች ወር” የሚል ትርጒም ይይዛል። ይህን ስያሜም ያገኘው በሀገራችን በአብዛኛው ሰርግ የሚደረገው በዚህ ወር  ስለሆነ ነው።

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህር ቤት ከተመሠረተበት ከ ፲፱፻፺፭ ዓ.ም. እስከ ፳፻፮ ዓ.ም. በባለቤትነት የአስተዳድረው የነበረው ማኅበረ ቅዱሳን ነበር፡፡ ከአገልግሎቱ እና መዋቅራዊ አደረጃጀት ባሕርይው አንጻር ሁለት መሠረታዊ ተግዳሮቶች ሲፈትኑት ቆይተዋል፡፡ የመጀመሪያው ለትምህርት ቤት የሚሆን የራሱ የሆነ ሕንፃ አለመኖር ሲሆን ሁለተኛው የሚፈለገውን የትምህርት ጥራት ለማምጣት የሚያስችሉ ግብዓቶችን ለማሟላት የሚያስችል የገንዘብ አቅም ማነስ ነው፡፡ ይህንን ችግር በዘለቄታው ለመፍታት ይቻል ዘንድ ማኅበረ ቅዱሳን፣ አባላቱ፣ የተማሪዎች ወላጆች እና የዓላማው ደጋፊዎች የሆኑ ግለሰቦች በጋራ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማኅበር (ኤስድሮስ በ፲፰ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአንድምታ ትርጓሜ መምህር የነበሩ ናቸው) በማቋቋም ከሐምሌ ወር ፳፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ የባለቤትነት ዝውውር ተደረገ፡፡ (የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መተዳደሪያ ደንብ)

ንጽሐ ጠባይዕ

ከአበው አንዱ “እግዚአብሔርን የማስደስተው ምን ባደርግ ነው? በጾም ነው? ወይስ በድካም ነው? ወይስ በምሕረት? ወይስ በትጋህ?” ብሎ ለጠየቀው ወንድም “አዎ፤ በእነዚህ ግብራት እግዚአብሔርን ደስ ልታሰኘው ትችላለህ። ነፍሳቸውንና ሥጋቸውን ያለ ዕረፍት ያደከሙ ብዙዎች እንደ ሆኑና ድካማቸው ግን ከንቱ እንደ ሆነ በእውነት እነግርሃለሁ። አፋችን መዓዛው እስኪለወጥ ድረስ አብዝተን ጾምን፣ የመጻሕፍትን ቃልም አጠናን፣ እግዚአብሔር የሚወደውን ፍቅርንና ትሕትናን ግን ገንዘብ አላደረግንም” በማለት ነበር የመለሰለት። ስለዚህ ለሁሉም መንፈሳዊ ተጋድሎዎችም ትጥቆችም መሠረትም ፍጻሜም ናት። ፍቅርንና ትሕትናን ገንዘብ በማድረግ ንጽሕ ጠባይዕን ገንዘብ ማድረግ የክርስትና ሕይወት መሠረት ነው። (ከበረሃውያን ሕይወትና አንደበት በመምህር ያረጋል አበጋዝ)

በሽተኛው ተፈወሰ!

ሕመም፣ በሽታና ክፉ ደዌ በሰዎች ሕይወት ውስጥ የሚያጋጥሙ የጤና እክሎች ናቸው፡፡ የሰው ዘር በሙሉ ከአዳም ጥፋት በኋላ ይህ ቅጣት እንደመጣበት ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡ አዳምና ሔዋን አትብሉ ተብሎ የነበረውን ዕፀ በለስ ከበሉ በኋላ ከደረሰባቸው መርገምት መካከል በሕመምና ሥቃይ እንዲቀጡ ነው፡፡ (ዘፍ.፫፥፲፮-፲፱)

ለምድራዊም ይሁን ለዘለዓለማዊው ሕይወታችን መገኘት፣ ድኅነትም ሆነ ፈውስ የሚገኘው በእግዚአብሔር አምላካችን ስናምንና ለእርሱ ስንታመን እንደሆነ ማወቅ ይገባል፡፡ መፃጉዕ ለጊዜው የተጠየቀው ነገር ከያዘው ደዌ እንዲድን ቢመስልም ጌታችን ግን የነፍሱንም ድኅነት ጠይቆታል፡፡ ‹‹ልትድን ትወዳለህን?›› ብሎ የጠየቀው ስለ እምነቱ ነበር፡፡ ከበሽታው ለመፈወስም እንኳን ቢሆን እምነት ከሌለ ሊድን እንደማይችል በቃሉ አስረድቶታል፡፡ ከዚያም አልፎ ተርፎ የነፍሱንም ነገር እንዲያስብ አሳስቦታል፡፡

ወርኃ መጋቢት

በመጋቢት ወር በኢትዮጵያ ዘንድ መዓልቱ እየጨመረ ሌሊቱ እያጠረ የሚሄድ ሲሆን የመዓልቱ ርዝመት ፲፪ ሰዓት የሌሊቱም ፲፪ ሰዓት ይሆናል። በክፍል በሚቆጥረው በሄኖክ አቆጣጠር ደግሞ የመጋቢት ወር መዓልቱ ዘጠኝ ክፍል ሌሊቱም ዘጠኝ  ክፍል እኩል ነው።

ወርኃ መጋቢት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ሰባተኛው ወር  ወርኀ መጋቢት ይባላል። መጋቢት በቁሙ “ስመ ወርኅ፣ ሳብዕት እመስከረም፣ የመዓልትና የሌሊት ምግብና ትክክል የሚሆንበት ወርኅ ዕሪና” ማለት ነው። “እስመ ይዔሪ መዓልተ ወሌሊተ አመ እስራ ወኀሙሱ ለወርኀ መጋቢት፤ በመጋቢት ወር ፳፭ ቀን ሌሊቱና መዓልቱ ይስተካከላልና” እንዲል፡፡ (ዲድስቅልያ ፴፣ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፭፻፸፯)

በዓለ ኪዳነ ምሕረት

ሰአሊተ ምሕረት፣ አቁራሪተ መዓት፣ ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ማኅደረ መለኮት፣ ብፅዕት፣ ከፍጥረት ይልቅ የተመሰገነች፣ እመ ብዙሃን፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለፍጥረት ሁለ ድኅነት ይሆን ዘንድ ከተወደደ ልጇ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን የተከበረች ናት፡፡