‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም›› (ድርሳነ ማርያም)

አብዛኛው ሰው ሲሞት ጻዕረ ሞት አለበት፤ ማቃሰት፣ ማጣጣር፣ የሞትን አስፈሪ ድምፅ መስማትም የተለመደ ነው፡፡ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን ይህ ሁሉ የለባትም፡፡ ቅዱስ ቶማስ ስለ አሟሟቷ ጠይቋት ነበር፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ ለመግለጽ አዳጋች ሆኖ እንጂ በርካታ ነገሮችን  ነግራዋለች፡፡ እናም ‹‹የሞት ጻዕር እንዴት አመመሽ›› ይላታል፡፡ እርሷም ‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም፤ ነፍሴ ያለ ድካም /ሕማም/ በደስታ ተለየች….›› በማለት ያለ ሕማም ያለ ድካም፣ ያለ ጭንቅ ያለ ጻዕርና ጋር በደስታ ነፍሷን ከሥጋዋ እንደተለየች ነግራዋለች፡፡ (ድርሳነ ማርያም ገጽ ፻፴፩)

ቃና ዘገሊላ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ሙሽራ አጊጣ፣ ለበጉ ሰርግ ያለ እድፍና ያለ ነውር ውብ ሆና ተዘጋጅታ በምትቀርብበት በዚያ ሰማያዊ ሰርግ ለመገኘትና ወደ በጉ ሰርግ ራት ገብተን፣ ካጌጡ ቅዱሳን ጋር ለመቀመጥና ለመብላት የበቃን ያድርገን፡፡

‹‹ወልድ ተውህበ ለነ›› (ኢሳ.፱፥፮)

ውድ ክርስቲያኖች! ይህ የሰው ልጅ ታሪክ የተቀየረበትን ዕለት በደስታ፣ በፍቅር፣ የተጣላን ታርቀን፣ የበደልን ክሰን፣ በኃጢአት ያደፈ ሕይወታችን በንስሐ አንጽተን፣ በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ሕይወታችንን አስቀድሰን እናክብረው!

መልካም በዓል!

ማኅበራዊ ሕይወታችን!

ተወዳጆች ሆይ! ስሙ እንደ መዓር በሚጣፍጥ፣ መድኃኒትም በሚሆን፣ በቅዱስነቱ ዘለዓለም ያለ ረዓድ በአስጨናቂዎቻችን ፊት ክብር እና ሞገስ አግኝተን፣ ሕያውም ሆነን በምንኖርበት በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዴት ሰነበታችሁ? ፍቁራን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ፈቃድ፣ በባሕርይ አባቱ በአብ፣ በባሕርይ ሕይወቱ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስም ፈቃድ ሳምንቱን አልፈን በቀጣይ ክፍል እነሆ ተገናኘን!

በባለፈው ሳምንት ስለ ማኅበራዊ ሕይወታችን፣ በእኛ ዘመን ምን እየሆነ፣ ምን እየሠራን እያለፍን እንደሆነ፣ ካለፈው ዘመን ጋር እያመሳሰልን ከራሳችን ጋር እየመዘንን በስሱም ቢሆን ገረፍ አድርገን ለማየት ሞክረናል። ዛሬም ያንኑ ርእሰ አንቀጽ ይዘን ማኅበራዊ ሕይወት በክርስትና አስተምህሮ እና በዘለዓለማዊ የሕይወት ሽግግራችን ያለውን ምልከታ፣ የማኅበራዊ ሕይወት መሳሳት መንሥኤዎችን እና መዳኛ የሚሆነንን ጠቅሰን እናልፋለን።

የእምነት አርበኞች!

ሕዝቡን እያሳተ ከገደል ቢመራ

ትእዛዙ ሲፈጸም ለሥጋው የፈራ

የእምነት አርበኖች ሠለስቱ ሕፃናት

ከፊቱ በመቆም መሰከሩ ለእምነት

በእሳት ሲያስፈራ በሚከስመው ነዶ

ጣኦትን ሊያስመልክ ፈጣሪን አስክዶ

ከላይ ከሰማያት መልአክን አውርዶ

እሳቱ ሲበርድ ሰይጣን በዚህ ሲያፍር

ጽናት ተጋድሏቸው ገሀድ ሲመሰክር

የጽድቅ ብርሃን

በብርሃናት ልብስ ተሸልሞ…
በብዙ ሀብታት ያጌጠ
ሥጋን ከነምኞቱ ሰቅሎ…
ለምትበልጠው ጸጋ ያለመታከት የሮጠ

ይህ ነው ዜና ማርቆስ ትውልድ የሚያወሳው
የጽድቅ ብርሃን… ጧፍ ሆኖ የሚያበራው!

ጽዮን ሆይ ክበቢኝ!

የገባልሽ ኪዳን የሰጠሽ መሐላ

ከንቱ ነበረ ወይ የጨረቃ ጥላ?

በአጋንንት ፍላጻ ነፍሴ ብትወጋ

ምልጃሽ ነው ተስፋዬ ከጥላሽ ልጠጋ፡፡

ጽዮን ሆይ ክበቢኝ ለውዳሴሽ ልትጋ

የኃጢአት ጎዳናዬ መንገዴ ይዘጋ!

እኔም ልመለስ!

እኔም ልመለስ ድንግል እናቴ
ከስደት ሕይወት ከባርነቴ
በልጅሽ ጉንጮች በወረደ ዕንባ
ባዘነው ልብሽ በተላበሰው የኀዘን ካባ
በእናት አንጀትሽ እንስፍስፍ ብሎ ያኔ በባባ

ልመለስ ድንግል ሆይ እኔም ከስደት
እውነትን ልያዝ ልራቅ ከሐሰት፡፡

ጥላቻ ገዝቶኝ ወንድሜን ከጠላው
እምነት ምግባሬን ሰይጣን ዘረፈው
መልሽኝ ድንግል ይብቃኝ ግዞቱ
በምግባር እጦት በቁም መሞቱ!

ከውድቀት አነሣን!

ለሰሚው በሚከብድ ቃላት በማይገልጸው

በመከራ ውሎ አዳምን አዳነው!

ዲያብሎስ ታሠረ አዳም ነጻ ወጥቶ

ልጅ ተባለ ዳግም በደሉ ተረስቶ

የማይሞተው አምላክ ስለ እኛ ሲል ሞቶ

ከውድቀት አነሣን ልጅነትን ሰጥቶ!

ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ

የአባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ተጋድሎ በጽኑ መሠረት ላይ በመገንባቱ የመከራ ዝናብ ቢዘንብ፣ የሥቃይ ጎርፍ ቢጎርፍ፣ የችግር ነፋስ ቢነፍስ አይወድቅም፡፡ (ማቴ.፯፥፳፭) ይህም የሆነው እነርሱን በመንፈሳዊ ሕይወት የተተከለ፣ በተጋድሎ ያሳደገ፣ ገቢረ ተአምራት ወመንክራት በማድረግ እንዲያብቡ ያደረገና ለፍሬ ክብር ያበቃ የክብር ባለቤት አምላካችንና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ ነው፡፡