‹‹የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት… ነው›› (ገላ.፭፥፳፪)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ጾመ ሁዳዴ (ጾመ ክርስቶስ) ሁለተኛው ሳምንት ላይ እንገኛለን፡፡ እሑድ ከወላጆቻችን ጋር ቤተ ክርስቲያን በመሄድ እያስቀደስን ነው አይደል? እንደ አቅማችን ደግሞ መጾምም አለብን! ከዚህ ቀደም ከምንጸልየው ጸሎት በተጨማሪ ጨምረን ልንጸልይም ይገባል!
በትምህርታችሁም በርቱና ተማሩ! ወላጆቻችን ከእኛ በጣም ብዙ ነገር ይጠብቃሉ፤ ጥሩ ውጤት እንድናመጣና ወደፊት ትልቅ ደረጃ እንድንደርስም ይመኛሉ፤ ታዲያ እኛ ስንፍናን አርቀን፣ ጨዋታን ቀንሰን፣ በርትተን በመማርና በማጥናት ጎበዝ ልጆች መሆን ይገባናል፤ መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ስለ መታዘዝ ተምረን ነበር፤ አሁን ደግሞ ስለ ትዕግሥት እንማራለን፡፡