[smartslider3 slider="3"]

ብፁዕ አቡነ አብርሃም እየተዳከመ የመጣው የብራና መጽሐፍ ዝግጅት ዳግም ማንሠራራቱን ገለጹ

ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት በኅዳር ፲፭፤ ፳፻፲፯ ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በአካሄደው የምስጋና መርሐ ግብር ላይ የተገኙት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ባስተላለፉት መልእክት የብራና መጽሐፍት ዝግጅት ረጅም ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ እየተዳከመ የመጣ ቢሆንም ዛሬ ላይ በዚህ መልክ እያደገ መምጣቱ የሚያስደስት መሆኑን አክለው ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎችን የሃይማኖት ነጻነት የሚጋፋ መመሪያ ማውጣቱ ተገለጸ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን የሚጋፋ መመሪያ መውጣቱን ገለጹ፡፡  ዮኒቨርስቲው በ፳፻፲፯ ዓ.ም ያወጣውን የሥነ ምግባርና ዲሲፕሊን መመሪያ ተከትሎ ይህንን መመሪያ ማውጣቱን ተማሪዎቹ አክለው ገልጸዋል፡፡

“የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል” (ማቴ.፳፬፥፯)

የምድር መናወጥ ወይም መንቀጥቀጥ በታሪክ መመዝገብ ከተጀመረበት ዘመን አንሥቶ እስከደረስንበት ዘመን ድረስ ከባድ የሚባል በሬክተር ስኬል ሰባት ነጥብ ሁለት እና  ከዚያ በላይ በዐሥርት ዓመታት ቢበዛ አንድ ጊዜ ነበር የሚከሠተው፡፡ ከ፲፱፻ ዓ.ም ወዲህ ግን ክብደቱም ብዛቱም የሚያደርሰውም ሰብአዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊና መሠረተ ልማታዊ ውድመቱና ጥፋቱ ጨምሯል፡፡ ከ ፲፱፻ እስከ ፲፱፻፵፱  በየዐሥርት ዓመቱ የሚደርሰው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ሦስት እና ከዚያ በላይ ሆኗል፡፡ በ፲፱፻፶ዎቹ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሮ ዘጠኝ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ በ፲፱፻፸ዎቹ ፻፳፭ አደገኛ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ ይህንን ሁኔታ ስንመለከተው ምድራችን በመሬት መንቀጥቀጥ ብዛትና ክብደት እየፈረሰች መሄዷ የማይቀር መሆኑን እንገነዘባለን፡፡