የሆሣዕና ምንባብ7(ማር. 10፥46-ፍጻ.)

 ወደ ኢያሪኮም ገባ፤ ከኢያሪኮም በወጣ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ከእርሱ ጋር ነበሩ፤ ብዙ ሰውም ነበረ፤ የጤሜዎስ ልጅ ዕውሩ በርጤሜዎስም በመንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን ነበር፡፡ የናዝሬቱ ኢየሱስ እንደ ሆነም ሰምቶ፥ “የዳዊት ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ማረኝ” ብሎ ጮኸ፡፡ ብዙዎችም ዝም እንዲል ገሠጹት፤ እርሱ ግን ድምፁን ከፍ አደረገና፥ “የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረኝ” አለ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ቆመና፥ “ጥሩት” አለ እነርሱም ዕውሩን ጠሩት፤ “በርታና ተነሥ፥ መምህር ይጠራሀል” አሉት፡፡ እርሱም ተነሥቶ ልብሱን ትቶ ወደ ጌታችን ኢየሱስ መጣ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፥ “ምን ላደርግልህ ትሻለህ?” አለው፤ ዕውሩም፥ “መምህር ሆይ፥ እንዳይ ነው” አለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም፥ “ሂድ፤ እምነትህ አዳነችህ” አለው፤ ወዲያውም አየ፤ በመንገድም ተከተለው፡፡