የዶዶላ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን አሁንም የጸጥታ ሥጋት እንዳለባቸው ተናገሩ

በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን የፀጥታ ሥጋት እንዳለባቸው ለዝግጅት ክፍላችን ተናገሩ፡፡

‹‹ወወፅኡ እምዐውድ እንዘ ይትፌሥሑ፤ ከሸንጐው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ››(የሐዋ. ሥራ ፭፥፵፩)

……እንግድህ ወደተነሣንበት ርእሳችን ስንመጣ ቅዱሳን ሐዋርያቱ በክርስቶስ ስም ከሚደርስባቸው መከራ ይልቅ ስለ ስሙ በሚቀበሉት መከራ የሚያገኙት ጸጋ እጅግ የሚበዛ መሆኑን በመረዳ ነውና ሁልጊዜም ከከሳሾቻቸው ፊት ደስ እያላቸው ይወጡ ነበር፡፡ በዚህ መከራቸውም በሞቱ መስለውታል የትንሣኤውም ተካፋዮች ሆነዋል፡፡

‹‹ፈለሰት ማርያም እምዘይበሊ ኀበኢይበሊ›› ቅዱስ ያሬድ

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ዓለም ፷፬ ዓመታትን በሕይወተ ሥጋ ከቆየች በኋላ ሥጋዋ በምድር እንዲቆይ የአምላክ ፈቃድ አልበነረም፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእናቱን ተድላ ነፍሷን እንጂ ተድላ ሥጋዋን አይወድምና ከጌቴሴማኒ ሥጋዋ ተነጥቆ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር እስከ ነሐሴ ዐሥራ ስድስት ቀን ለሁለት መቶ አምስት ቀናት እንድትቆይ ፈቃዱ አደረገ፡፡ እርሱ ሞትን በሥልጣኑ እንዳሸነፈ ሁሉ በልጇ መለኮታዊ ኃይል ሞትን አሸንፋ ተነስታለች፡፡

የሀዋሳ ማእከል ሕግና ዕቅበተ እምነት ዋና ክፍል ተጠሪ የነበሩት አቶ አስማማው ታመነ አረፉ

በማኅበረ ቅዱሳን የሀዋሳ ማእከል ሕግና ዕቅበተ እምነት አገልግሎት ዋና ክፍል ተጠሪ የነበሩት አቶ አስማማው ታመነ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በደረሰባቸው ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸው እንዳለፈ የሀዋሳ ማእከል አስታወቀ፡፡

‹‹ሦስቱ የጥፋት ገመዶች እንዳይጥሏችሁ ተጠበቁ!›› አቡነ ተክለ ሃይማኖት

ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት በተጋድሏቸው ዘመን በአባ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለዐሥር ዓመት በነበሩበት ጊዜ አገልጋዮቹ ወደ እርሳቸው መጥተው ይመክሯቸው ዘንድ ለመኗቸው፤ እርሳቸውም ‹‹ትዕግሥትን፣ ትሕትናን እና እግዚአብሔርን መፍራት ገንዘብ አድርጉ፤ እነዚህ ሦስት ነገሮች ሰውን ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት ያደርሱታል፡፡ እየጎተቱ ወደደይን ጥልቅነት የሚያወርዱ ሦስቱ የጥፋት ገመዶች እርሳቸውም ቅናት፣ ትዕቢትና ትምክሕት እንዳይጥሏችሁ ደግሞ ተጠበቁ›› ብለው መከሯቸው፡፡ (ገድለ ተክለ ሃይማኖት  ፵፫፥፬-፮)