ዐቢይ ጾም

ዐቢይ ጾም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ ከተጠመቀ በኋላ ዐርባ ቀን የጾመው፤ እኛም እንድንጾማቸው በቤተ ክርስቲያናችን ከታዘዝናቸው ሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዱ ነው፡፡ ምእመናን ጌታችን ያደረገውን ምሳሌ ተከትለን ጾሙን በየዓመቱ እንጾመዋለን፡፡ ዐቢይ ጾም ስምንት ሳምንታት (፶፭ ቀኖች) አሉት፡፡ በውስጡ ስምንት ቅዳሜዎች፣ ሰባት እሑዶች ይገኛሉ፡፡ ይኸውም ዐሥራ አምስት ቀን ማለት ነው፡፡ እነዚህ ቀናት ከጥሉላት እንጂ ከእህል ውኃ ስለማይጦሙ የጦሙ ወራት ዐርባ ቀን ብቻ ይሆናል፡፡

‹‹ለተቀበሉት ሁሉ ግን÷ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው›› (ዮሐ. ፩፥፲፪)

የክርስቶስ አካል እንደመሆናችን መጠን ደግሞ ይህን ኃላፊነት በተለያየ መልኩ በሕይወታችን ልንተገብር እንደሚገባ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ክርስቲያኖች ከአምላካቸው የተቀበሉትን ትእዛዝ መፈጸምም አለባቸው፡፡ ወላጆች ልጆቻቸውን በልጅነት ጥምቀት በማስጠመቅ፣ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት በማሳደግ እና ሥርዓተ አምልኮቱን እንዲፈጽሙ በመርዳት ማሳደግ አለባቸው፡፡ ይህንንም መጀመር ያለባቸው ልጆቹ ሰባት ዓመት ሲሞላቸው እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ላይ ተጠቅሷል፡፡

በኢትየጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ወቅታዊ ችግር አስመልክቶ ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

ልጆችሽ

ቅድስት ማርያም (ባለሽቶዋ) እንተ ዕረፍት

ጌታችንም በስምዖን ቤት እንደ ግብፃውያን አቀማመጥ እግሩን ወደኋላ አድርጎ ነበር፤ አንድም ወንበሩ እንደ አፍርንጆች ወንበር እግር ወደኋላ የሚያደርግ ነው፤(ወንጌል ቅዱስ) እርሷም ከአጠገቡ ስትደርስ ከእግሩ በታች ከሰገደች በኋላ ‹‹በስተኋላውም በእግሩ አጠገብ ቆማ እያለቀሰች በእንባዋ እግሩን ታርስ ጀመረች፤ በራስ ጠጉሯም ታብሰው፣ እግሩንም ትስመው፣ ሽቱም ትቀባው ነበረች፡፡›› (ሉቃ.፯፥፴፰-፴፱)

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም

በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የረጅም ዘመን ሐዋርያዊ ጉዞ ላይ በጎ ተፅዕኖ ካላቸው የአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አባቶች መካከል አንዱ ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም ነው፡፡ ይህ አባት ምንም እንኳን በቋንቋ ውሱንነትና በቦታ ርቀት በርካቶች ሥራዎቹና ጽሑፎቹ የታወቁለት ባይሆንም ሕይወቱን በብሕትውና የመራ የትርጓሜ መጻሕፍትን፣ የቅኔ፣ የግጥምና የወግ ጽሑፍ በማዘጋጀት የኖረ አባት ነው፡፡

ጾመ ሰብአ ነነዌ

‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሦስት ቀን ጾም የጾሙት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው (ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪)፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የሆነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶ ነበር (ዮናስ ፬፥፲፩)፡፡

የኢትዮጵያውያን ቅዱሳት አንስት አርአያነት

የቅዱሳት አንስት ገድል እንደ አርአያና ምሳሌ ሆኖ ለብዙ ምእመናን ትምህርት ሊሆን የሚችል ታሪክ ነው። የእነዚህም አንስት ተጋድሎ እንደየዘመናቱ ቢለያይም ለሕዝቡ ካለው ሚና አንጻር ሁሌም አስፈላጊነቱ የላቀ ነው፡፡

ሥርዓተ ንባብ

ውድ አንባብያን በአለፈው ትምህርታችን ከምንባቡ ላይ ተነሽ ንባባትን እንድትጽፉ መልመጃ መስጠታችን ይታወቃል። እንደሠራችሁትም ተስፋ እናደርጋለን። ለማረጋገጥ ያህል ምንባቡንና መልሱን እንደሚከተለው እናቀርባለን።