የሐዋሳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ችግር ፊጥረዋል ባላቸው ላይ ውሳኔ አሳለፈ

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
በከሳሽ የሐዋሳ ከተማ አቃቤ ሕግ እና በሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተፈጠረው ግጭት ከፍተኛ የአካል ጉዳት አድርሰዋል ተብለው በተከሰሱት በሐዋሳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተካሄደው ክርክር ውሳኔ አገኘ፡፡

ትናንት ግንቦት 25 ቀን 2003 ዓ.ም በዋለው ችሎት በከሳሽ የሐዋሳ ከተማ አቃቤ ሕግ በኩል የሰውና የተለያዩ ማስረጃዎች የቀረበ ሲሆን ተከሳሾቹ መከላከል እንዳልቻሉ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡
ከግራና ከቀኝ ክርክሮችን ያደመጠው ችሎት የተስፋ ኪዳነ ምሕረት ሰብሳቢ በሆነው ገዛኸኝ አበራ ላይ የ8 ዓመት፣ አየነው ወ/ሚካኤል ላይ 8 ዓመት፣ አቶ ተስፋዬ ገ/መድህን ላይ የ3 ዓመት እንዲሁም ጌታሁን ተፈራ ላይ የ5 ዓመት የእስራት ብይን ሰጥቷል፡፡
ተከሳሾቹ ምንም ዓይነት የመፀፀትና የመመለስ አዝማሚያ ባለማሳየታቸው ቅጣቱ ሊከብድባቸው እንደቻለ ተገልጿል፡፡
በተያያዘም አዲስ የተሾሙት የሲዳማ አማሮ ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሥራ አስኪያጅ ትናንት ወደ ተመደቡበት ሀገረ ስብከት ደርሰዋል፡፡