የሆሣዕና ምንባብ11(ማር.11÷1-12.)
ኢየሩሳሌም ለመግባት በደብረ ዘይት አጠገብ ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ በደረሱ ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ላከ፡፡ እንዲህም አላቸው÷ “በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፤ ወደ መንደርም በገባችሁ ጊዜ÷ ሰው በላዩ ያልተቀመጠበት የአህያ ውርንጫ ታስሮ ታገኛላችሁ፤ ፍቱና አምጡልኝ፡፡ ‹ምን ታደርጋላችሁ?› የሚላችሁ ሰው ቢኖርም ‹ጌታው ይሻዋል› በሉ፤ ወዲያውኑም ወደዚህ ይሰድደዋል፡፡” ሄደውም በበሩ አጠገብ ባለው ሜዳ በመንገድ ዳር የታሰረ ውርንጫ […]