ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና

ጥር ፳፤፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና

ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና

ፀንሳው በድንግልና

ወልዳውም በድንግልና

ሆነች ማኅደረ መለኮት

በምድር ለተገኘው በከብቶች በረት

አዝላው ተጓዘች በግብጽ ውዕየት

ጭው ባለውም በረኀና ሙቀት

የሌቱን ቁርና ውኃ ጥማት

ተቋቁማ አለፈች ብርዱና ሙቀት

ሁሉን ተቀበለች ለሰዎች ድኅነት

ሆናለች እናቱ ለዓለም መድኃኒት

ደረሶ መፈጸሚያው ያ ተስፋው ቃል

አንዴ ሊሰቀል አካላዊ ቃል

በእውነት ተቀበለ መከራ መስቀል

ግን ጭንቅና ኀዘን ሆኖባት እናቱ

አምርራም አለቀሰች በመሠቃየቱ

አንዲያ ልጇን አይታ ሲሰቅሉት

በጭካኔ ታውረው በትዕቢት

አጽናኝም አጣች ፍጹም ሥቃይ ሆኖባት

ዳግምም መነሣቱን ወዳም ልትታገሥ

ጠብቃ ለማየት የናፈቃትን ልጇን ኢየሱስ

እንደተናገረውም ተነሥቶ ክርስቶስ

ቆመላት ፊቷ ለሐዋርያት ሞገስ

በዚያም ተጽናንታ በምድር ኖረችበት

የአምላክ እናት ለ፷፬ ዓመታት

አብዝታ በመመላለስ ሳታቋርጥ ጸሎት

በጌቴሴማኒ መቃብሩ ቤት

ጊዜው ደረሰና ከተወደደው ልጇ የምትሄድበት

ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና

ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና