የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ የቀብር ሥነ ሥርዓት የቀጥታ ዘገባ

ነሐሴ 16 ቀን 2004 ዓ.ም.

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}kebre{/gallery}
  • 4፡00 የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ አስከሬን አርፎ ከሰነበተበት ከሐያት ሆስፒታል ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የደብር አስተዳዳሪዎች ካህናትና ቀሳውስት የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዘምራን ዘመድ አዝማድና ምእመናን ታጅቦ ጠቅላይ ቤተ ክህነት  ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ደረሰ፡፡

  • 4፡30 አስከሬኑ በመንበረ ፓትርያርክ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ካረፈ በኋላ መርሐ ግብሩ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎት ተጀመረ፡፡

  • 4፡36 በርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ካህናት ጸሎተ ወንጌል እየተደረሰ ነው፡፡

  • 4፡50 በብፁዕ አቡነ ናትናኤል መሪነት ጸሎተ ኪዳን እየተደረሰ ነው፡፡

  • 4፡57 በስብከተ ወንጌል አዳራሹ የነበረው መርሐ ግብር ተጠናቆ የቅዱስነታቸው አስከሬን ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ቅድስት ማርያም ገዳም እየተወሰደ ነው፡፡

  • 8፡30 ጸሎተ ቅዳሴው ተጠናቋል፡፡ በተያዘው መርሐ ግብር መሠረት የቅዱስነታቸው አስከሬን በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የአድባራት አለቆች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራንና ምእመናን እንዲሁም ክቡራን እንግዶች ታጅቦ ወደ ወንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጉዞ ጀምሯል፡፡

  • 9፡50 የቅዱስነታቸው አስከሬን በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የአድባራት አለቆች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራንና ምእመናን እንዲሁም ክቡራን እንግዶች ታጅቦ ወደ ወንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል  እያመራ ሲሆን አሁን አራት ኪሎ አደባባይ ደርሷል፡፡

  • 10፡25 የቅዱስነታቸው አስከሬን በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካትድራል በክብር ደርሷል፡፡