የማኅበሩን አገልግሎት ለማገዝ የማእከላት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ተመሠረቱ

የካቲት 9/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደጀኔ

በማኅበረ ቅዱሳን ለሀገር ውስጥ ማእከላትና የግቢ ጉባኤያት ማ/ማስተባበሪያ ዋና ክፍል ተጠሪ የሆኑ 6(ስድስት) ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች ተቋቋሙ፡፡

ማኅበሩ አገልግሎቱን ይበልጥ አጠናክሮ ለማገልገል የተሰጠውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ሓላፊነት ለመወጣት የማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን ነው የተገለጸው፡፡

መቀመጫቸው የሰሜን ማእከላት ማስተባበሪያ በመቀሌ፣ የሰሜን ምዕራብ ማእከላት ማስተባበሪያ በባሕርዳር፣ የምዕራብ ማእከላት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በጅማ፣ የደቡብ ማእከላት ማስባበሪያ ጽ/ቤት በአዋሳ የምሥራቅ ማእከላት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በድሬደዋና የመሀል ማእከላት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አዲስ አበባ ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡

ጥር ፳6 እና ፳7 ቀን ፳፻4 ዓ.ም ማእከላት የማስተባበሪያ ጽ/ቤት ምስረታ ላይ የማስተባበሪያ ጽ/ቤት የሚያካልላቸው ማእከላት በተገኙበት ተመስርተዋል፡፡ በምስረታ መርሐ ግብሩ ላይ የማስተባበሪያ ማእከላቱ ጽ/ቤት ተግባርና ሓላፊነት እንዲሁም የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት በማኅበረ ቅዱሳን ምን መምሰል አለበት በሚሉ ርዕሰ ጉዳይ የስልጠናና የውይይት መርሐ ግብር ተካሔዷል፡፡

15 አባላት ያሉት የማስተባበሪያ ጽ/ቤት አስፈጻሚ አካላት የሀገር ውስጥ ማእከላትና ግቢ ጉባኤያት ማደራጃና ማስተባበሪያ ዋና ክፍል ጨምሮ በዋና ማእከል ከሚገኙ ዋና ክፍሎች ጋር ግንኙነት በማድረግ ለሚከናወኑ ተግባራት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር እንደሚሠሩ ይጠበቃል፡፡