[smartslider3 slider="3"]

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

ቅዱስነታቸው በጥር ፳፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የሰጡት የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ

ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና እና እስልምና በኢትዮጵያ

በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል እየተዘጋጀ የሚቀርበው የጥናትና ምርምር ጉባኤ ታኅሣሥ 22/2015 ዓ.ም በማኅበሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ 3ኛ ፎቅ በርካታ ምእመናን በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በዕለቱ ሁለት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፤ ከእነዚህም “ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና እና እስልምና በኢትዮጵያ ዕቅበተ እምነታዊ ጉዳዮች” በሚል የቀረበው አንዱ ነው። ኢትዮጵያ ሀገራችን በ6ኛ መ/ክ የነበራት ግዛትና ተጽእኖ እስከ ዓረቢያን ምድር የሰፋ እንደነበረ የተለያዩ ድርሳናት እንደሚመሰክሩ በጥናቱ መግቢያ ተጠቁሟል። ይህን የግዛት ወሰን ተከትሎ በአቅራቢያ ከሚገኙ የዓረብ ሀገራት ጋር በተለያዩ መንገዶች ለመገናኘት በር ከፍቷል።