ነገረ ክርስቶስ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ

በአቤል ሚካኤል
ብርህት፣ ንጽህት፣ ጽድልት፣ የሆነች ቤተክርስቲያናችን ከምታስተምራቸው ትምህርቶች አንዱና ዋነኛው ነገረ ክርስቶስ ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ትምህርት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ሥላሴ አንዱ አካል ወልድ ሲሆን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የተካከለ ሲሆን በኋላኛ ዘመን ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ሰው ሆነ፡፡