• እንኳን በደኅና መጡ !

“አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፤ አንተና የመቅደስህ ታቦትም” (መዝ. ፻፴፩፥፰)

በመምህር ሳሙኤል ተስፋዬ እግዚአብሔር አምላካችን አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም “ከልጅ ልጅህ ተወልጄ ስደትህን በስደቴ፣ ሞትህን በሞቴ አጥፍቼ፤ የቀደመ ክብርህን መልሼ ያጣኸውን ርስት፣ ገነትን (መንግሥተ ሰማያትን) አወርስለሁ” በማለት ለአባታችን አዳም የገባው ቃል ኪዳን ፍጻሜው በደረሰ ጊዜ ለእግዚአብሔር ወልድ ማደሪያነት የተመረጠች፣ ለአዳም እና ለዘሩ መዳን ምክንያት የኾነች “የልጅ ልጅ” የተባለችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡ ፲፭ ዓመት ሲኾናት በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት የእግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ማደሪያ ኾነች (ገላ. ፬፥፬)፡፡ ልጇን በወለደች ወቅት “የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት አለ?”  የሚለውን የሰብአ ሰገልን ዜና […]

“ሠናይ ውእቱ ለነ ሀልዎ ዝየ” (ማቴ.፲፯፥፬)

በዲ/ን ዐቢይ ሙሉቀን የቃሉ ተናጋሪ የሐዋርያት አለቃ ቅዱስ ጴጥሮስ ነው። ቃሉን የተናገረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን ሊገልጥላቸው ከነቢያት ሙሴንና ኤልያስን፣ ከሐዋርያት ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ወደ ተራራው ባወጣቸው ጊዜ ነው፡፡ ሙሴና ኤልያስ ከክርስቶስ ጋር ሲነጋገሩ ሰምቶ “በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው፣ ብትፈቅድስ ሦስት ሰቀላዎች እንሥራ አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ” በማለት […]

ሱባኤያችን በረከት የሚያሰጥ ይሁን

በእንዳለ ደምስስ በረከትን በመሻት በፍልሰታ ለማርያም ጾም ሱባኤ ለመያዝ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በታነጸውና በቤተ ክርስቲያናችን ከሚታወቁ ታላላቅ ገዳማት ወደ አንዱ ለመሔድ ዝግጅት ሳደርግ ቆይቻለሁ፡፡ ወደ ንስሓ አባቴ ቀርቤ ንስሓ ገብቼና ቀኖናዬን ተቀብዬ፣ ከመሥሪያ ቤቴ ደግሞ ፈቃድ ቀኑ ሲደርስ በዋዜማው የሚያስፈልጉኝን የጸሎት መጻሕፍት፣ አልባሳት፣ በሶና ጥሬ ሽምብራ በቦርሳዬ ሸክፌ፣ የጸበል መቅጃ አነስተኛ ጀሪካን አንጠልጥዬ […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን