• እንኳን በደኅና መጡ !

ጸሎተ ኀሙስ

ከመምህር አዲሱ በዛብህከስቅለትና ከትንሣኤ በፊት በሕማማት ሳምንት ያለው ሐሙስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ ስያሜዎች አሉት፡፡ እነዚህንም ስያሜያት እንደሚከተለው እንመለከታለን።ሀ. ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ይለምን ይማልድ የነበረን ሥጋ የተዋሐደ ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰው መሆኑን ለማጠየቅ እንዲሁም ለአርአያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪዙት ድረስ ሲጸልይ በማደሩ ምክንያት ይህንን ስያሜ አገኘ። (ማቴ ፳፮፥፴፮-፵፮፣ ፲፯፥፩)ለ. ሕጽበተ እግር […]

ረቡዕ

እያንዳንዱ የሰሙነ ሕማማት ዕለታት ስያሜ እንዳላቸው ዕለተ ረቡዕም ራሱን የቸለ ምሥጢራዊና ታሪካዊ ትርጒም አለው፡፡ ይህም እንደሚከተለው በዝርዝርእንመለከታለን።የምክር ቀን (ምክረ አይሁድ)አይሁድ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስሰ ክርስቶስን የሚይዙበትን መንገድ ይፈልጉ ነበር፤ በመካከላቸው ምንም ዓይነት ልዩነት እንኳን ቢኖር ለኃጢአት ሥራ ግን ተባበሩ፡፡ ፰ት ለተለያየ አላማ የተቋቋመ ማኅበር (ስምንቱ ቤተ አይሁድ) ፦ ሊቃነ ካህናት፣ መገብተ ምኲራብ፣ ኃጥኣን መጸብሓን፣ ጸሓፍት ፈሪሳውያን፣ […]

ሰሙነ ሕማማት ሠሉስ

ከመምህር ተፈሪ መንገሻ በኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት የሰሙነ ሕማማት ዕለታት የየራሳቸው ስያሜና ምሥጢር አላቸው። ከእነዚያ መካከል ዕለተ ሠሉስ የትምህርት ቀን የጥያቄ ቀን በመባል ይታወቃል። ይህንንም አስመልክቶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በዕለቱ ጌታ ረጅም ትምህርት ያስተማረበትና ከአይሁድ፣ ከጸሓፍትና ከፈሪሳውያን ብዙ የተንኮል ጥያቄዎችን ተቀብሎ ለእነርሱም በጥበብ መልስ የሰጠበትን ድንቅ ትምህርት ሥርዓት ሠርታ ትዘክራለች/ታስታውሳለች። ይህች ዕለት የሰው ልጅ ውሱን በሆነው […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን