• እንኳን በደኅና መጡ !

“በእንተ ልደታ ለማርያም ፍስሐ ኮነ” (ቅዱስ ያሬድ)

“ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ግንቦት ፩ ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከአባቷ ኢያቄምና ከእናቷ ቅድስት ሐና መወለዷን ትመሰክራለች፡፡ (ስንክሳር ግንቦት ፩፣ ተአምረ ማርያም)፡፡ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነቢያት በልዩ ልዩ አገላለጽ በትንቢትና በምሳሌ መስለው ተናግረዋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት “በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች” (መዝ. ፵፬፥፱) በማለት የተናገረላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል […]

ዳግም ትንሣኤ

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዐርብ ተሰቅሎ፣ በሦስተኛውም ቀን መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል በዝግ መቃብር ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣና በትንሣኤው ትንሣኤአችንን ካወጀልን በኋላ ሐዋርያት በአንድነት ተሰብስበው ሳለ ተገልጦላቸዋል፡፡ ይህንንም ወንጌላውያኑ በመተባበር ገልጸውታል፡፡ በተለይ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ “ያም ከሳምንቱ የመጀመሪያው ቀን በመሸ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ አይሁድን ስለ ፈሩ ተሰብስበው የነበሩበት ቤት ደጁ ተቆልፎ ሳለ ጌታችን […]

ከትንሣኤ ማግሥት እሰከ ዳግም ትንሣኤ የቀናት ስያሜዎች

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ማግስት አንሥቶ እስከ የሚቀጥለው እሑድ (ዳግም ትንሣኤ) ያሉትን ቀናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለእያንዳንዳቸው ዕለታት ስያሜ ሰጥታ ታስባቸዋለች፡፡ እነዚህንም ቀጥለን እንመለከታቸዋለን፡፡ ፩. የትንሣኤ ማግሥት/ ሰኞ ማዕዶት (ሽግግር) ወይም ፀአተ ሲኦል ነፍሳት ከሲኦል እሥራት ነጻ መውጣታቸው እንዲሁም ከሞት ወደ ሕይወት መሸጋገራቸው የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለ፶፻፭፻ (አምስት ሺህ አምስት መቶ) ዘመን […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን