• እንኳን በደኅና መጡ !

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ጥንተ ስቅለቱ መታሰቢያ በዓል አደረሳችኹ።

ጥቅምት ሃያ ሰባት በዚህች ዕለት የአምላካችን የመድኃኔዓለም የስቅለቱ መታሰቢያ ነው። መድኃኒታችን ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና በቸርነቱ ስለኹላችን ድኅነት ሲል ራሱን ወድዶ ፈቅዶ ለሞት አሳልፎ በመስጠት ፍጹም ፍቅሩን አሳይቶናል። በቅዱስ ወንጌልም እርሱም መድኃኒታችን “ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለም” ብሎ ነግሮናል። እውነት ነው፣ ራስን አሳልፎ ከመስጠት በላይ ምን ድንቅ ነገርና ምን ድንቅ ፍቅር አለ? ቸሩ አምላካችንን የአስቆሮቱ ይሁዳ […]

እግዚአብሔር የመረጠው ጾም

  ለተወሰነ ሰዓት ከምግበ ሥጋ የመከልከላችን ዓላማ ራሳችንን መግዛት እንድንችል ነው፡፡ ስለዚህ ‘እየጾምኩ ነው’/የሚል ሰው ካለ ከምንም በፊት ትዕግሥተኛ ፣ ልበ ትሑትና የዋህ ፣ እግዚአብሔርን የሚፈራ ልቡና ያለው ፣ የፍትወታትን ጅረት ከኹለንተናው የሚያስወግድ ፣ ዘወትር በልቡናው ዕለተ ምጽአትን የሚያስብ ፣ በእግዚአብሔር የፍርድ ዙፋን ፊት እንደሚቆም የማይረሳ ፣ በፍቅረ ንዋይ ወጥመድ ተይዞ ምጽዋትን የማይጠላ፣ ወንድሙን ከልቡ የሚወድ ይኹን፡፡ እውነተኛ ጾም ማለት ይኽ ነውና፡፡

ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ

¹ በዓለ ሐምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥

² ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው።