• እንኳን በደኅና መጡ !

ይ ቅ ር ታ

በአንዲት ሀገር አንድ ንጉሥ ነበር ። ይህ ንጉሥ በቤተ-መንግስት ውስጥ ብዙ አገልጋዮች አሉት – ያሉት አገልጋዮችም ምንም አይነት ስህተት እንዲሰሩ አይፈቅድም ። ትንሽ ጥፋት ሲያጠፉ ተለይቶ በተዘጋጀው ስፍራ ሰው እያያቸው ታስረው በተራቡ ጨካኝ የጫካ ውሾች ተበልተው እንዲሞቱ ያደርግ ነበር ። ከእለታት በአንዱ ቀን ንጉሡን ለ25 ዓመታት ያገለገው ባርያ ጥፋት ያጠፋና በንጉሡ ፊት ያቀርቡታል ። ንጉሡም በውሾች ተበልቶ እንዲሞት ፈረደበት ። ይህ ባርያ በተፈረደበት ፍርድ ከመሞቱ በፊት አሥር ቀን በቤተ-መንግስት ውስጥ እንዲያገለግል ንጉሡን ለመነ እናም ተፈቀደለት ።

ኃጢአተኛዋ/ውን ማረኝ

በድሮ ዘመን ወንጀል የሚሠሩ አመጸኞች ተይዘው ሲታሰሩ በግራና ቀኝ እጃቸው መቅዘፊያ ይዘው በጉልበታቸው ኃይል እየቀዘፉ የመንግስትን መርከቦች በባህር ላይ እንዲነዱ ይገደዱ ነበር።

አንድ ቀንም አንድ ንጉሥ ክፉ ሥራ የሠሩ ወንጀለኞች ታሥረው ወደ ሚገኙበት መርከብ ገባ። እስረኞቹም የታሰሩበትን ከባድ ሰንሰለት ሲመለከት እጅግ አዘነላቸው። በልቡም “ከእነዚህ አንዱን ልፍታ” ሲል አሰበ።

የዘይቱ ነገር

  አንድ ሰው በጣም የሚወደው ልጅ ነበረው፡፡ ለዚህ ልጁ ሕይወትን ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብሮ እንዴት መኖር እንደሚችል ሊያስተምረው ይጥር ነበር፡፡ ነገር ግን ብዙም የተሳካለት አልመሰለውም፡፡ ልጁ በፊቱ የመጣለትን ነገር በማድረግ የሚነዳና ምንም አይነት መንፈሳዊነትና ጥበብ የሞላው ሕይወት እንዳላዳበረ ገባው፡ በአካባቢው በጥበቡ የታወቀ አንድ አባት ነበረና የሕይወት ጥበብ እንዲማር ወደዚያ ጠቢብ አባት ላከው፡፡

በፌስቡክ ያግኙን