እ ን ኳ ን ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አ ደ ረ ሳ ች ሁ።

ተአምራትን በሚያደርግ በከበረ በቅዱስ ሚካኤል በዓል ቀን መታሰቢያን የሚያደርግ ኹሉ ለቤተክርስቲያን ዕጣን የሚሰጥ ቢኾን መስዋዕትን የሚያቀርብ ቢኾን የተራበውን ያበላ የተጠማውን ያጠጣ ቢኾን የታረዘም ያለበሰ ቢኾን ያዘነውን ያረጋጋ የተከዘውን ደስ ያሰኘ የታመመውን የጎበኘ ቢኾን ስለከበረ ስለ መላእክት አለቃ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ስም በጭንቅ በመከራ ያለውን እሥረኛን የጠየቀም ቢኾን ገሃነምን አያያትም።

በዚኽ ዓለም እግዚአብሔር ከበጎ ነገር ኹሉ አያሳጣውም። በሞተ ጊዜም ነፍስን እያካሰሱ ወደ ሲዖል የሚያደርሱ አጋንንት በሰማይ በር ሊከራከሩት አይችሉም።

ይኸው ቅዱስ ሚካኤል በብሩሃን ክንፎቹ ተሸክሞ የእሳት ባሕርን ያሻግረዋል። በልዑል እግዚአብሔር ዙፋን ፊት ያቆመዋል። ነፍስ ለልዑል እግዚአብሔር ትሰግዳለች። ከዚኽ በኋላ ወደ ተድላ ገነት ይወስዳታል። እርሱ ራሱ ጌታችን በማይታበል ቃሉ ተናግሯልና። ለወዳጆቹም ኹሉ ቃል ኪዳን ሰጥቶአቸዋልና እንዲኽ ብሎ ከወዳጆቼ ጋር ቃል ኪዳን አደረግኹ።”

† ድርሳነ ሚካኤል †

ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ልዑል ዘተሳተፈ ፣ ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ጸሐፈ ፣ ሶበ እጼውእ ስመከ ከሢትየ አፈ ፣ ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ ፣ ለረዲኦትየ ነዓ ሰፊሐከ ክንፈ ።

የቅዱስ ሚካኤል ምልጃና ረዳትነቱ አይለየን