• እንኳን በደኅና መጡ !

የሚከራከርልን መምህር

መምህር ዘየዐሲ፥ መምህር ዘይትቃወም ለነ (የሚሰጥ መምህር፥ የሚከራከርልን መምህር) ጌታችን ዋጋ የሚሰጥ መምህር ነው። ከዚህ ዓለም መምህር ሲለይ የሚሰጥ መምህር አለ፤ የዚህ ዓለም መምህር ሲያስተምር ውሎ “ይደልዎ አስቦ ለዘይትቀነይ፤ ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋል”[ሉቃ. ፲÷፯] ይላል ብሎ ዋጋ ይቀበላል እንጂ አይሰጥም። እርሱ ግን ይሰጣል እንጂ አይቀበልምና አንድም ሃይማኖት አስይዞ ምግባር አሠርቶ የዚያን ዋጋ የሚሰጥ መምህር እርሱ ነው። […]

ሆሣዕና

ሆሣዕና የሚለው ቃል በዕብራይስጥ ሆሼዕናህ የሚል ሲሆን ትርጉሙም እባክህ አሁን አድን ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል በዘመነ ብሉይ በቀደምት ነቢያት ዘንድ የተለመደ ቃል ነው። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ “ኦ እግዚኦ አድኅንሶ፤ ኦ እግዚኦ ሠርሕሶ፤ ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር [አቤቱ እባክህ አድነን፤ አቤቱ ጎዳናችንን(መንገዳችንን) አቅና፤ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩከ ነው]” እንዳለ።  መዝ. ፻፲፯፥፳፭-፳፮። ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም ሰንበታት […]

ኒቆዲሞስ

  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ እንኳን ለዐቢይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት (ኒቆዲሞስ) አደረሳችሁ/አደረሰን። ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር መጥቶ በመዋዕለ ሥጋዌው በኪደተ እግር ከቦታ ቦታ እየተመላለሰ የምስራቹን ቃል ሲያውጅ እስራኤላውያን የተቀበሉት በተደበላለቀ ስሜት ነበር። በአንድ በኩል ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ሲገዛ ስለነበር ከሮማውያን ቅኝ ግዛት ነጻ የሚያወጣቸው መሲህ […]