መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የቃለ ዓዋዲው ማሻሻያ ረቂቅ ይመከርበት!
መስከረም 30 ቀን 2005
ሰበካ ጉባኤ በካህናትና በምእመናን ኅብረት ላይ የቆመ መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ሥርዐት ነው፡፡ ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ባሉት መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ በየደረጃው አመራር ይሰጣል፣
ዕቅድ ያወጣል፣ ውሳኔ ያሳልፋል፡፡ ጉባኤው ቤተ ክርስቲያናችን ከመሬት ስሪት ተነሥታ በሕዝብ ባለቤትነት ላይ የተመሠረተችበትና ሕጋዊ ሰውነት ያገኘችበትም የሕግ አካል ነው፡፡
ዘመነ ጽጌ
በ44ቱ የሀገር ውስጥ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤ ይደረጋል
መስከረም 28 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደጀኔ
ማኅበረ ቅዱሳን በሀገር ውስጥ አገልግሎቱን ለማፋጠን ባቋቋማቸው 44 ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤ እንደሚያካሂድ ተገለጸ፡፡
መስቀል (ለሕፃናት)
መስከረም 22 ቀን 2005 ዓ.ም
ቢኒያም ፍቅረ ማርያም
ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት ዕርቅና ሰላም መሠረት ናቸው
መስከረም 22 ቀን 2005 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዘመኑ የተለያዩ ፈተናዎች የተፈራረቁባት ሲሆን ቤተ ክርስቲያኒቱ የእግዚአብሔር ማደሪያ ነችና የመጣውን የፈተና ጎርፍና ነፋስ ሁሉ ተቋቁማ አሁን ላለንበት ዘመን ደርሳለች፡፡ የዐላውያን ገዢዎችን ሰይፍ ከውስጥም ከውጭም የነበሩ መናፍቃንን ቅሰጣ ተሻግራ እስከአሁን የሐዋርያትን፣ የቅዱሳን ሊቃውንትን የአትናቴዎስን የቄርሎስን ሃይማኖት ይዛ ተገኝታለች፡፡፡ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን የሚመጡባትን ፈተናዎች የምታደንቅ፣ በዚያም ተስፋ የምትቆርጥ አይደለችም፡፡ ሁል ጊዜም ቢሆን የገሃነም ደጆች የሚሰብቁት ግልጽና ስውር ጦር እንዳለ ስለምታውቅ ከሚመጣው ፈተና ሁሉ አሸንፋ ትወጣ ዘንድ ወደ አምላኳ ትለምናለች እንጂ፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ትእምርተ ሰላም
መስከረም 21 ቀን 2005 ዓ.ም.
በኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ከሃይማኖት አክራሪነት ጋር በተያያዘ አንዳንድ ግጭቶች መከሰታቸው ይታወቃል፡፡ መንግሥትም ለችግሩ መፍትሔ ለመስጠት ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ የአብዛኛዎቹ የ”ግጭት” ጠባይ ግን የተለየ ነበር፡፡ የሁለት እምነት ተከታዮች በመፎካከርና በመወዳደር ወይም ደግሞ ከተራ ጥላቻና ግለሰባዊ ግጭት አንሥተው ሃይማኖታዊ ያደረጉት አልነበረም፡፡
ከዚያ ይልቅ በአንድ ወገን ያሉት በማያውቁትና ባላሰቡት ሰዓት የደረሰ ድንገተኛ አደጋ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ጥቃቱን የፈጸሙትም የሚከተሉትን ሃይማኖት አባቶች ወካዮችና ከዚያው ከቤተ እምነታቸው ተከታዮች ሙሉ ይሁንታ አግኝተው የተላኩ አልነበሩም፡፡ ይህን የማድረግ ዓላማ ብቻ ሳይሆን በቂ ዝግጅትና ጥናት ያደረጉ የሃይማኖት አክራሪዎች መሆናቸው ከድርጊታቸውም፤ ከተገኘውም ማስረጃ ግልጽ ነበር፡፡
መጪውን ጊዜ በሃይማኖት “ብሔርተኝነት” መዋጀት
መስከረም 18 ቀን 2005 ዓ.ም.
ጊዜ ይመጣል ጊዜ ይሄዳል፡፡ ጊዜ መጥቶ ሲሄድ ግን እንደው ዝም ብሎ አይደለም፡፡ የጊዜውን አሻራ አሳርፎ ነው፡፡ አሻራው ግን አዎንታዊም አሉታዊም ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ምርጫው በጊዜ መጠነ ክበብ ውስጥ ያለው የሰው ልጅ ነው፡፡
የሰው ልጅ ደግሞ በጊዜያት ውስጥ የረቀቀና የገዘፈ ዓለም ባለቤት ሆኖ የተፈጠረና ጊዜ የማይቆጠሩላቸው የሥሉስ ቅዱስ ፍጡር ነው፡፡ በሕያውነቱ ረቂቁን ዓለም- ዓለመ ነፍስን መስሎና ሆኖ ሲኖር፤ በምድራዊነቱ ግዙፉን ዓለም- ዓለመ ሥጋን በተዋሕዶ ነፍስ መስሎና ሆኖ ይኖራል፡፡ በዚህም የሁለት ዓለም ባለቤት ነው፡፡ የሰማያዊና ምድራዊ ወይም የመንፈሳዊና ዓለማዊ፡፡
የማኅበሩ የቴሌቪዥን መርሐ ግብር ሰዓት ወደፊት የሚሻሻል መሆኑ ተገለጠ
መስከረም 16 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
ማኅበረ ቅዱሳን ባሳለፍነው ሳምንት ማጠናቀቂያ የቴሌቪዥን መርሐ ግብርን በኢትዮጵያ ብሮድ ካስቲንግ ሰርቪስ ቴሌቪዥን (EBS TV) ለመጀመር ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቁንና ይህንኑ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ አስተያየታቸውን እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የማኅበሩ አባላት፣ ካህናትና ምእመናን፡- ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ በመጣው የማኅበሩ አገልግሎት ከልብ መደሰታቸውን አስታውቀው፤ ነገር ግን የተመረጠው ጊዜ ሕዝበ ክርስቲያኑ ከቤተ ክርስቲያን ከሚወጣበት ሰዓት ጋር በጣም መቀራረቡ ፣ በተጨማሪም አጠቃላይ የመርሐ ግብሩ ጊዜ በ30 ደቂቃ መገደቡ እንዳሳሰባቸው ገልጠውልናል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዠን መርሐ ግብር ሊጀምር ነው
መስከረም 12 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ማኅበረ ቅዱሳን ከጥቅምት 4 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር በየሳምንቱ እሑድ ጧት ከ3፡30 እስከ 4፡00 ሰዓት የሚቆይ መርሐ ግብር በኢትዮጵያ ብሮድ ካስቲንግ ሰርቪስ ቴሌቪዠን (EBS TV) ለመጀመር ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቁ ተገለጠ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጠ
መስከረም 12 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በቤተ ክርስቲያኒቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መስከረም 11 ቀን 2004 ዓ. ም. መግለጫ ሰጠ፡፡ መግለጫውን የሰጡት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊ የሆኑት እስክንድር ገብረ ክርስቶስ ሲሆኑ በመግለጫቸውም “በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥና ዙሪያ ተሸሽገው የተዛባ መረጃን በማቀበል የሽግግር ወቅት ሂደቱን ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዳይራመድ የሚጥሩ ወገኖች ሁሉ ከዚህ አፍራሽ እንቅስቃሴያቸው እንዲታቀቡ እያሳሰብን ይህ ባይሆን ግን የሽግግር ሂደቱን ሰላማዊ ለማድረግ ሲባል ቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ እርምጃዎቸን ለመውስድ የምትገደድ መሆኑን አጥብቃ ለማሳሰብ ትወዳለች፡፡” ብለዋል፡፡