አገልግሎቴን አከብራለሁ!

በእያንዳንዳችን ሕይወት ውስጥ “አገልግሎት” የሚለው ቃል በተለያየ መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ሰው በግሉ፣ ከቤተ ሰቡ እንዲሁም ከማኅበረሰቡ ጋር ከሚያከናውናቸው ተግባራት ውስጥ “አገልግሎቴ” ብሎ የሚያስባቸው ምግባሮች ሊኖሩት ይችላሉ፡፡ ለዚህም ዕውቀት ይኑረው አይኑረው ለማወቅ ቢያዳግትም ከቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ግን አገልግሎትን ማወቅ፣ መረዳትና መተግበር እንዲችል ግንዛቤ መፍጠር ተገቢ ነው፡፡

ወርኃ ታኅሣሥ

ሰፊ አስተምህሮ እና ምሥጢር ካላቸው ወራት አንዱ የታኅሣሥ ወር ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ በባሕረ ሐሳብ ቀመር ቀኑ ዘጠኝ ሌሊቱ ዐሥራ አምስት ይሆናል፤ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጨመረ ሌሊቱ እያነስ ይሄዳል

ምድር እስከ መቼ ታለቅሳለች?

ምድር ዛሬ እያለቀሰች ነው፡፡ ግን እስከ መቼ ታለቅሳለች? ሰዎችስ ከክፋታቸው የሚመለሱት መቼ ነው? የምድረ በዳው ሣርስ እስከ መቼ ደርቆ ይቀጥላል? አዕዋፋትና እንስሳትስ እስከ መቼ ያልቃሉ? እግዚአብሔርስ ምድርን እስከ መቼ ነው የሚቆጣት? ቅዱሳንስ ስለ ደማቸው እስከ መቼ ምድርን ይካሰሷታል? ነቢዩ ኤርምያስ የሚጠይቀውን ጥያቄ አሁንም እኛ እንጠይቃለን፡፡

ወርኃ ኅዳር

ሦስተኛው ወር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት “ኅዳር” ተብሎ ይታወቃል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል ሲተረጉሙ “ማኅደር” ከሚለው ሥርወ ቃል የወጣ እንደሆነና “ማደሪያ” የሚል ፍቺ እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡

“የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል” (ማቴ.፳፬፥፯)

የምድር መናወጥ ወይም መንቀጥቀጥ በታሪክ መመዝገብ ከተጀመረበት ዘመን አንሥቶ እስከደረስንበት ዘመን ድረስ ከባድ የሚባል በሬክተር ስኬል ሰባት ነጥብ ሁለት እና  ከዚያ በላይ በዐሥርት ዓመታት ቢበዛ አንድ ጊዜ ነበር የሚከሠተው፡፡ ከ፲፱፻ ዓ.ም ወዲህ ግን ክብደቱም ብዛቱም የሚያደርሰውም ሰብአዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊና መሠረተ ልማታዊ ውድመቱና ጥፋቱ ጨምሯል፡፡ ከ ፲፱፻ እስከ ፲፱፻፵፱  በየዐሥርት ዓመቱ የሚደርሰው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ሦስት እና ከዚያ በላይ ሆኗል፡፡ በ፲፱፻፶ዎቹ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሮ ዘጠኝ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ በ፲፱፻፸ዎቹ ፻፳፭ አደገኛ የመሬት መንቀጥቀጦች ደርሰዋል፡፡ ይህንን ሁኔታ ስንመለከተው ምድራችን በመሬት መንቀጥቀጥ ብዛትና ክብደት እየፈረሰች መሄዷ የማይቀር መሆኑን እንገነዘባለን፡፡

ወርኃ ጥቅምት

የጥቅምት ወርን በተመለከተ መጽሐፈ ስንክሳር በወርኃ ጥቅምት ንባብ መግቢያው “የጥቅምት ወር የቀኑ ሰዓት ዐሥራ አንድ ነው፤ ከዚህም በኋላ ይቀንሳል” ይላል፤ ይህም ማለት በቀን ውስጥ ካለው ሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የሌሊቱ ሰዓት ዐሥራ ሦስቱን ሲይዝ የቀኑ ጊዜ ደግሞ ዐሥራ አንዱን ሰዓት ይይዛል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በጥቅምት ወር የሌሊቱ ጊዜ ቀኑ ጊዜ ይረዝማል ማለት ነው፡፡

ጥቅምት ቃሉ “ጠቂም ጠቂሞት” ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም “የተሠራች፣ ሥር” ማለት ነው፤ ዓለም የተፈጠረው በዚህ ወር በመሆኑ “ጥንተ ግብር (የሥራ መጀመሪያ)” ማለት ነው፡

ጥቅምት የሚለውን ቃል ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲተረጉሙ “ስመ ወርኅ፣ ካልእ መስከረም፣ ጽጌውን መደብ አድርጎ ፍሬ፣ ወርኃ ፍሬ፣ መዋዕለ ሰዊት ይሰኛል” ይላሉ፡፡ (መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ፭፻፰)

የጥያቄዎቹ ምላሾች

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? አዲሱ ዓመት እንዴት ነው? ዘመን መለወጫን አከበርን፤ ከዚያም የመስቀልን በዓል አከበርን፤ ደስ ይላል አይደል! አሁን ደግሞ ትምህርት ጀምራችኋልና መበርታት ይገባል፡፡ እንግዲህ ከአሁኑ ጀምራችሁ መምህራን የሚሰጧችሁን ትምህርት በንቃት ተከታተሉ! መጻሕፍትን አንብቡ፤ ምክንያቱም አሁን ካላጠናችሁ በኋላ ፈተናዎችን ማለፍ ይከብዳችኋል!

ታዲያ ልጆች! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርንም እንዳንዘነጋ! በሰንበት ሄደን በመማር በሥነ ምግባር ያጌጠ፣ በሃይማኖቱ የጸና ጎበዝ ተማሪ ሆኖ ማደግ ያስፈልጋል፤ መልካም! ዛሬ  ባለፈው ለጠየቅናችሁ ጥያቄዎች ምላሹቹን እንነግራችኋለን! አንብባችሁ ምላሽ የሰጣችሁ በርቱ! ያልመለሳችሁ ደግሞ በቀጣይ በምናዘጋጀው ጥያቄና መልስ ተሳተፉ!

ዘመነ ጽጌ

በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከመስከረም ፳፮ ጀምሮ ያለው ጊዜ ዘመነ ጽጌ፣ ወርኃ ጽጌ እየተባለ ይጠራል፡፡ ጽጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን በእነዚህ ሰሞናት የሚዘመሩ መዝሙራት፣ የሚነበቡ ምንባባት ምድር በጽጌያት ማሸብረቁን የሚገልጡ ናቸው

ዘካርያስ

የመስከረም ወር የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አባት ዕረፍት የሚታሰብበት ወር ነው፡፡ መስከረም ፰ ቀን ደግሞ የበራክዩ ልጅ ካህንና ነቢይ የነበረ ዘካርያስ በሄሮድስ እጅ በሰማዕትነት ያረፈበት ነው፡፡

ወርኃ መስከረም

መስከረም ለሚለው ቃል መነሻ “ከረመ” የሚለው ግስ ነው፤ ትርጓሜውም “ቀዳማይ፣ ለዓለም ሁሉ መጀመሪያ፣ ርእሰ ክራማት፣ መቅድመ አውራኅ” የሚለውን ያመለክታል፡፡ በሌላ በኩል መስከረም የመጀመሪያ ወር ስም፣ ከዘመነ ሥጋዌ በፊትም ለዓለም ሁሉ የመጀመሪያ ወር ማለት ነው፤ “መስ” የሚለው ቃልም መነሻ መስየ የሚለው ግስ ሲሆን “ምሴተ ክረምት (የክረምት ምሽት) በምሥጢር ደግሞ ፀአተ ክረምት (የክረምት መውጫ)፣ የክረምት ጫፍ መካተቻ፣ የመፀው መባቻ” መሆኑን ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላታቸው ይገልጣሉ፤ (ገጽ ፮፻፲፪) እንዲሁም “መቅድመ አውራኅ (የወራት መጀመሪያ) ርእሰ ክራማት” ይሰኛል ይላሉ፡፡