ንጽሐ ጠባይዕ
ከአበው አንዱ “እግዚአብሔርን የማስደስተው ምን ባደርግ ነው? በጾም ነው? ወይስ በድካም ነው? ወይስ በምሕረት? ወይስ በትጋህ?” ብሎ ለጠየቀው ወንድም “አዎ፤ በእነዚህ ግብራት እግዚአብሔርን ደስ ልታሰኘው ትችላለህ። ነፍሳቸውንና ሥጋቸውን ያለ ዕረፍት ያደከሙ ብዙዎች እንደ ሆኑና ድካማቸው ግን ከንቱ እንደ ሆነ በእውነት እነግርሃለሁ። አፋችን መዓዛው እስኪለወጥ ድረስ አብዝተን ጾምን፣ የመጻሕፍትን ቃልም አጠናን፣ እግዚአብሔር የሚወደውን ፍቅርንና ትሕትናን ግን ገንዘብ አላደረግንም” በማለት ነበር የመለሰለት። ስለዚህ ለሁሉም መንፈሳዊ ተጋድሎዎችም ትጥቆችም መሠረትም ፍጻሜም ናት። ፍቅርንና ትሕትናን ገንዘብ በማድረግ ንጽሕ ጠባይዕን ገንዘብ ማድረግ የክርስትና ሕይወት መሠረት ነው። (ከበረሃውያን ሕይወትና አንደበት በመምህር ያረጋል አበጋዝ)