በዓለ ኪዳነ ምሕረት

ሰአሊተ ምሕረት፣ አቁራሪተ መዓት፣ ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ማኅደረ መለኮት፣ ብፅዕት፣ ከፍጥረት ይልቅ የተመሰገነች፣ እመ ብዙሃን፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለፍጥረት ሁለ ድኅነት ይሆን ዘንድ ከተወደደ ልጇ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን የተከበረች ናት፡፡

“ስለ ምን ጾምን?” (ኢሳ.፶፰፥፫)

የነነዌ ከተማ ሰዎች ኃጢአት በትንቢተ ዮናስ ውስጥ አንድ ሁለት ተብሎ አልተገለጸም፤ በጥቅሉ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ” ተብሎ በእግዚአብሔር ከመገለጹ በቀር አልተዘረዘረም። (ዮናስ ፩፥፪) ሆኖም ክፉታቸው ወደ ፊቴ ወጥቶአልና የሚለው የልዑል አምላክ ቃል የኃጢአታቸውን ታላቅነት ያመለክታል። ኃጢአታቸው በዮናስ መጽሐፍ ውስጥ አልተዘረዘረም አልን እንጂ በሌሎቹ መጻሕፍት ውስጥ ግን ተዘርዝሯል። ለምሳሌ ነቢዩ ናሆም የነነዌ ኃጢአት ምን ምን እንደነበረ ገልጿል። እነዚህም፡-

ወርኃ የካቲት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ስድስተኛው ወር “የካቲት” ተብሎ ይታወቃል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል “ከተተ” ከሚለው ግስ ከወጣው “ከቲት፣ ከቲቶት” ከሚል ንኡስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን በቁሙ “የወር ስም፣ ስድስተኛ ወር፣ የመከር ጫፍ (መካተቻ)፣ የበልግ መባቻ ማለት ነው” ብለው ተርጉመውታል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፭፻፲፭)

ሌሎችም ጸሐፍያን “የካቲት” የሚለው ቃል “ከቲት፣ ከቲቶት” ከሚል የግእዝ ንኡስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን “መውቃት፣ ማምረት፣ መሰብሰብ፣ መክተት” የሚል ትርጉም ይኖረዋል ካሉ በኋላ ይህንም ስም ያገኘው የካቲት ወር አዝመራ (ምርት) ወደ ጎተራ የሚከተትበት ወራት በመሆኑ ነው ብለዋል። (ኅብረ ኢትዮጵያ፣ ከቴዎድሮስ በየነ፣ አዲስ አበባ ፲፱፻፺፱ ዓ.ም፡፡ አንድሮ ሜዳ፣ ገጽ ፫፻፺፭፣ አቡሻክር የጊዜ ቀመር፣ በኢንጅነር አብርሃም አብደላ ገጽ ፵፱) በቁጥር ትምህርት አንዱ ወር በባተበት የትኛው ወር እንደሚብት በቃል የሚጠና ሲሆን የካቲት በባተችበትም ጳጕሜን እንዲሁም የካቲት በባተበት ሳኒታ ሰኔ ይብታል፡፡

‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም›› (ድርሳነ ማርያም)

አብዛኛው ሰው ሲሞት ጻዕረ ሞት አለበት፤ ማቃሰት፣ ማጣጣር፣ የሞትን አስፈሪ ድምፅ መስማትም የተለመደ ነው፡፡ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ግን ይህ ሁሉ የለባትም፡፡ ቅዱስ ቶማስ ስለ አሟሟቷ ጠይቋት ነበር፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ ለመግለጽ አዳጋች ሆኖ እንጂ በርካታ ነገሮችን  ነግራዋለች፡፡ እናም ‹‹የሞት ጻዕር እንዴት አመመሽ›› ይላታል፡፡ እርሷም ‹‹መልአከ ሞት አልነካኝም፤ የጨለማው አበጋዝም አልደረሰብኝም፤ ነፍሴ ያለ ድካም /ሕማም/ በደስታ ተለየች….›› በማለት ያለ ሕማም ያለ ድካም፣ ያለ ጭንቅ ያለ ጻዕርና ጋር በደስታ ነፍሷን ከሥጋዋ እንደተለየች ነግራዋለች፡፡ (ድርሳነ ማርያም ገጽ ፻፴፩)

‹‹ምድር በውስጧ የሚኖሩትን ታስደነግጣቸዋለች›› (ዕዝራ ሱቱኤል ፬፥፳፬)

ዛሬ የምድር መሠረቶች እየተናወጡ ነው፡፡ ሕይወት ያለውን ፍጡር ሁሉ መድረሻና ጥግ ያሳጣ ፈተና በምድር ላይ እየታየ ነው፡፡ ምድር እንደ ዛፍ የምትወዛወዝበት፣ እሳት የምትተፋበት፣ ሊቆሙባት፣ ሊተኙባት የምታስጨንቅና የምታስደነግጥ ሆናለች፡፡ ይህም በሰው ልጆች ዓለም ውስጥ አስጨናቂው ጊዜ ነው፡፡ ሰዎች ከፍተዋል፤ ተፈጥሮም ከፍታለች፤ ሰዎች ፈጣሪንና ተፈጥሮን በድለዋል፤ እግዚአብሔርና ተፈጥሮ ደግሞ የቁጣቸውን ጅራፍ አንሥተዋል፡፡ ይህም የዘመኑ ፍጻሜ ስለመድረሱ አመላካችም እንደሆነ መልአኩ እንዲህ ሲል ነግሮታል፡፡ ‹‹ተነሥተህ በእግርህ ቁም፤ ጩኸት የተሞላበትን ቃል እነግርሃለሁ፡፡ መነዋወጥ አንተ የቆምህበት ቦታ ቢነዋወጽ መነዋወጹ የኅልፈት ምልክት ነውና፡፡ ያን ጊዜ የምድር መሠረቶች የኅልፈትን ምልክት ያስረዳሉ›› በማለት፡፡ (ዕዝ.፬፥፲፬)

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርተ ወንጌልን በቃሉ አስተምሮ እንዲሁም ለሐዋርያት ቃሉን በዓለም እንዲዘሩ ‹‹ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ለፍጥረትም ሁሉ ወንጌልን ስበኩ›› ብሎ ባዘዛቸው መሠረት ወንጌል በምንኖርባት ምድር ለዘመናት ስትሰበክ ኖራለች፡፡ (ማር.፲፮፥፲፭) ጻድቃን አባቶቻችንም ለእኛ ሐዲስ ኪዳን ሰዎች ቃሉን በአደራ እንዳስረከቡንም በተመሳሳይ መልኩ ለልጆቻችንና ለልጅ ልጆቻችን የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረን በሃይማኖትና በክርስቲያናዊ ምግባር ኮትኩተን ማሳደግ ኃላፊነችን ነው፡፡

ወርኃ ጥር

በባሕረ ሐሳብ ቀመር መሠረት ቀኑ ዐሥር ሰዓት ሲሆን ከዚህ በኋላ ሌሊቱ እየጨመረ ይሄዳል። ጥር የሚለው ስያሜ “ጠር፣ ጠይሮ፣ ጠየረ፣ ጠሪእ፣ (ጠርአ፣ ይጠርእ፣ ጸርሐ) ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጒሙም “መጥራት፣ መጮኽ፣ አቤት ማለት” ነው፡፡ (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፭፻፲) ጥር የወር ስም ሆኖ በታኅሣሥ ወር እና በየካቲት ወር መካከል የሚገኝ፣ ከዐሥራ ሦስቱ ኢትዮጵያ የወራት አቆጣጠር ውስጥ አምስተኛው ነው።

በዚህም ወር ዘመነ አስተርእዮ ይታሰባል፤ አስተርእዮ በጥሬ ትርጉሙ “መገለጥ” ነው፤ ይህም ወቅት በዋናነት ስውር የነበረ ምሥጢረ ሥላሴ የተገለጠበት፣ ሰማያዊ አምላክ በኩነተ ሥጋ ለድኅነተ ዓለም ሲል በዚህ ዓለም የተገለጠበት፣ ሰማያዊ ምሥጢርም የታየበት ድንቅና ልዩ ዘመን ነውና እንዲህ ተብሎ ተጠራ።

ምድር እስከ መቼ ታለቅሳለች?

እውነት ነው! ደም በከንቱ ፈስሶ አይቀርም፡፡ የንጹሐን ደም ዋጋ ያስከፍላል፤ ልጅን የልጅ ልጅን ያጠፋል፤ ከርስት ከጉልት ይነቅላል፤ እሳትና ዲን ያዘንማል፤ ምድርንም ያቃጥላል፡፡ እነዚህ ሁሉ ዛሬ እንደዘበት የሚገደሉ ነፍሳት ሁሉ ክሳቸው አይቋረጥም፤ ቃላቸውም እስከ ሰማየ ሰማያት ያስተጋባል፤ የገዳዮች ልጆች ከዚህ ምድር እስኪጠፉ፣ የልጅ ልጆቻቸውም ከሰው ልጅ ተለይቶ እስኪጠፋ ትውልዳቸውም እስኪደመሰስ ነፍሳት ይካሰሳሉ፤ የነፍሳት ጌታም እውነተኛ ዳኛ ነውና፤ ፍትሕ ርትዕ አያጎድልምና፤ ፍርዱን በምድርና በውስጧ ባለን በሁላችን ላይ ያመጣል፡፡ ሰማያትን ይለጉማል፤ ምድርን ያናውጣታል፤ ጠለ ምሕረትን እክለ በረከትን እንዳታስገኝ ፣ የመዓት ነፋሳት እንዲነፍሱና መቅሠፍት እንዲሆኑ፣ ዝናማት በረዶ እንዲሆኑ አድርጓል፡፡ ልንመለስ አልወደድንምና፡፡

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

በእያንዳንዳችን ሕይወት ውስጥ “አገልግሎት” የሚለው ቃል በተለያየ መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ሰው በግሉ፣ ከቤተ ሰቡ እንዲሁም ከማኅበረሰቡ ጋር ከሚያከናውናቸው ተግባራት ውስጥ “አገልግሎቴ” ብሎ የሚያስባቸው ምግባሮች ሊኖሩት ይችላሉ፡፡ ለዚህም ዕውቀት ይኑረው አይኑረው ለማወቅ ቢያዳግትም ከቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ግን አገልግሎትን ማወቅ፣ መረዳትና መተግበር እንዲችል ግንዛቤ መፍጠር ተገቢ ነው፡፡

ወርኃ ታኅሣሥ

ሰፊ አስተምህሮ እና ምሥጢር ካላቸው ወራት አንዱ የታኅሣሥ ወር ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ በባሕረ ሐሳብ ቀመር ቀኑ ዘጠኝ ሌሊቱ ዐሥራ አምስት ይሆናል፤ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጨመረ ሌሊቱ እያነስ ይሄዳል