ተጠያቂው ማነው?

መምሬ እውነቱ ከንስሓ ልጆቻቸው ጋር በመሆን ሕሙማንን ለመጠየቅ በያዙት መርሐ ግብር መሠረት ከምእመናኑ ተወካዮች እና ከማኅበረ ካህናቱ ተወካዮች ጋር የተቃጠሩበት ሰዓት እስኪደርስ ከግቢያቸው ካለው ዛፍ ሥር ተቀምጠው ሌሎቹን በመጠበቅ ላይ ናቸው፡፡

‹‹አትጨነቁ…›› (ማቴ.፮፥፴፬)

ሰዎች  መልካምና ክፋ ነገርን ለማሳካት ይጨነቃሉ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹አትጨነቁ›› ያለን ለክፋትና ለኃላፊው ዓለም ተጨንቀን መፍትሔ ለማናመጣለት ነገር ነው፡፡ (ማቴ.፮፥፴፬) ፈጣሪያችን ለእኛ ለልጆቹ በዚህ ምድር በእንግድነት ስንኖር ምን እንደሚያስፈልገን ያውቃል፤ የሚያሻንንም ይሰጠናል፤ እናስብ ዘንድ አስተዋይ አእምሮ ሰጥቶናል፤ ማሰብ ከሚገባን በላይ ደግሞ ልንጨነቅ ስለማይገባ ‹‹አትጨነቁ›› አለ፡፡ አበው በብሂላቸው ‹‹…አስብ እንጂ አትጨነቅ..›› የሚሉን ለዚህ ነው፡፡ በምድር ስንኖር በማሰብ በመጠንቀቅ፣ በመጠበቅ እንደ ርግብ የዋህ እንደ እባብ ደግሞ ብልህ ሆነን ልንኖር ያስፈልጋል፡፡ ልንፈራና ልንጨነቅ እንደማይገባ ግን ክርስትናችን ያስተምረናል፡፡ ጌታችን ለአባቶቻችንን ቅዱሳን ሐዋርያት ስለሚቀበለው መከራ፣ ስለሞቱ ሲነግራቸው ባዘኑ ጊዜ ‹‹…ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም ደግሞ እመኑ…›› በማለት በአንዳች ነገር እንዳይጨነቁ ልባቸው እንዳይታወክ ነገራቸው፡፡ (ዮሐ. ፲፬፥፩)

የቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ካርታ

ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! እንደምንከረማችሁ? እንደምን ሰነበታችሁ? የዛሬ የዚህ ክፍለ ጽሑፍ ዓላማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የመጭው ዐሥር ዓመታት የመንፈሳዊ እና ዘላቂ ልማት ግቦችን ማስተዋወቅ ነው፡፡

የቤተ ክርስቲያንን የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በዝርዝር ከመዳሰሳችን በፊት ዕቅድ ምን እንደሆነና የዕቅድን አስፈላጊነት በትንሹ መዳሰስ አስፈላጊ ነው፡፡

“እግዚአብሔርን የምትወዱ ክፋትን ጥሉ” (መዝ.፺፯፥፲)

በባሕርይው ፍጹም፣ ቅዱስ፣ ንጹሕ የሆነና ምንም ዓይነት ርኩሰት የማይስማማው አምላካችን እግዚአብሔር መልካም አባት ነው፡፡ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድሞ የነበረ፣ አሁን ያለ ወደ ፊትም ዓለምን አሳልፎ የሚኖር በመሆኑም ለዘለዓለም በቅድስና ይኖራል፡፡ ፍጥረቱን በሙሉም በቸርነቱ ከመፍጠሩ በፊት ሲቀደስ ሲለስ ይኖር የነበረ፣ አሁንም በፍጥረቱ እንዲመሰገን፣ እንዲቀደስ፣ እንዲወደስ የፈቀደ፣ ወደፊት ደግሞ በክብር ምስጋና በመንግሥቱ ሊገዛ የሚወድ ፈጣሪያችን ክብሩንና ቅድስናውንም ለፍጥረቱ በተለይም ለቅዱሳን መላእክት እና ሰው የሚያደርግ ነው፡፡ ይህን ሁሉም በቸርነቱ፣ በመልካምነቱ፣ በበጎነቱ፣ ስለ ቅዱስ ፈቃዱ አድርጓል፡፡

ቅድስት ሥላሴ በአብርሃም ቤት

በሐምሌ ሰባት ቀን እግዚአብሔር አምላክ በአብርሃም ቤት ተገኝቶ እንደባረከው ቅን ልቡና ያላቸውን፣ ለጋሾች ለሆኑ፣ ምጽዋትን ለሚያቀርቡ፣ እንግዳ መቀበል የዘወትር ልማዳቸው ላደረጉ ሰዎች በቤታቸው ይገባል፡፡ የተዘጋውንም ማኅፀን እንደከፈተ ቤቱንም እንደባረከ አይተናል፡፡ ዛሬም እኛም ለተራቡ በማብላት፣ ለተጠሙ በማጠጣት፣ ለታረዙ በማልበስ፣ በመመጽወትና በመሳሰለው ተግባር መኖር፣ በቀና አስተሳሰብ መጓዝ እንዳለብን መጽሐፍ ይነግረናል፡፡

ወርኃ ሐምሌ

ሐምሌ የወር ስም ሲሆን ሐምል “ሐመልማል” ከሚለው ግስ የተገኘ ነው፤ “ሐምል” ማለት “ቅጠል፣ ቅጠላ ቅጠል፣ ሣር፣ ቋያ፣ ቡቃያ፣ ተክል” ማለት ሲሆን ሐምሌ ማለት ደግሞ ቅጠላም ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፬፻፵፱)

ወሩ ስያሜውን ያገኘው ምድር የሰማይ ጠልን ስታገኝ በእርሷ ላይ ከሚታየው ተፈጥሮአዊ ለውጥ የተነሣ ነው፤ በበጋው ወራት ደርቃና ተሰነጣጥቃ የነበረች ምድር በክረምቱ መግቢያ የሚዘንበው ዝናብ ድርቀቷን አስወግዶ ሲያለሰልሳት ልምላሜ ይታይባታል፡፡ ሣሩ፣ ቅጠሉ በቅሎ በአረንጓዴ ዕፅዋት ተውባ የክረምቱን መግባት የበጋውን ማብቃት ታበሥርበታለች፡፡

ፍረጃና መዘዙ

ፍረጃ አንድን አካል ወይም ሰው ማንነቱን የማይገልጠው ስም፣ እውነታን ባላገናዘበ መልኩ ግላዊና ማኅበረሰባዊ በሆነ መንገድ ለሰዎች ስያሜ መስጠት ፣ ከአንድ ጉዳይ ተነሥቶ ሁሉን መጥላትና ማንቋሸሽ ነው፡፡ ፍረጃውን የሚያደርጉ ሰዎችም ፍረጃውን መሠረት አድርገው በክፉ የፈረጁት ግለሰብ ወይም ቡድን አንዳች ቅጣት እንዲደርስበት ስለሚፈልጉ ለዚያ ፍረጃና ቅጣት ምስክር አድርገው የሚያቀርቡት እውነታን ሳይሆን የራሳቸውን ትርክት ነው፡፡ ፍረጃ ሰዎችን ለማግለልና ለመነጠልም እንደ መሣሪያ ሆኖ የሚያገለግልና በቀላሉ የማይነቀልም ሂደት/ቀጣይነት ያለው ነው፡፡ ፍረጃውን ለሚያደርጉ ሰዎችና ፍረጃቸውንም ለሚቀበሉ ሰዎች በፈረጇቸው ሰዎች ላይ ከሕግና ከሥርዓት ወጥተው የራሳቸውን ፍርድ በመስጠት ከድብደባ እስከ ግድያ የሚደርስ ወንጀል እንዲፈጽሙ ያደርጋቸዋል፡፡

እግረ ኅሊና

ጉባኤ ዘርግተው በዐውድ ምሕረት ላይ በተመስጦ ቅዱስ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሲያስተምሩ የሰሚው በጎ ፈቃድና እዝነ ልቡና ከእነርሱ ጋር እንደሆነ በማመን ነው፡፡ የሕይወት ማዕድ ተዘጋጅቶ ሲቀርብም ታዳሚው ሊቋደስ የተገባ በመሆኑ በጆሮአችንም ሆነ በእዝነ ልቡናችን ሰምቶ መቀበል ድርሻችን ነው፡

“መባዬን በመያዝ ወደ ቤትህ እገባለሁ” (መዝ.፷፭፥፲፫)

ድንቅ በሆነ ሥራው ዓለምን ከእነ ጓዟ ለፈጠረ አምላክ የሚበቃ ከሰው ዘንድ የሚሰጥ ምን ነገር ይኖራል? ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ባለ ጸጋው አምላካችን ልናቀርብስ የምንችለው ከእኛ የሆነ ከእርሱ ዘንድ ዋጋ ያለውስ ነገር ምን ይሆን? እርሱ ባወቀና በፈቀደ ከእርሱ የሆነ ግን ከእኛ የሚሰጥ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ስጦታን እንድናቀርብ ግን ተሰጠን፡፡ “ለከበረ ስምህም ከአንተ የተገኘውን ዕጣን አቀረብንልህ” እንዲል፡፡ ሁሉ በእጁ ለሆነው አምላክ ስጦታ እንድናቀርብም ክቡር ፈቃዱ ሆነልን፡፡

የተቀደሰ ውኃ

“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ። ምድርም ባዶ ነበረች፥ አንዳችም አልነበረባትም፤ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር።” (ዘፍ.፩፥፩-፪)