ነቢያት ለምን ጾሙ?

ኅዳር ፲፭፤፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

የአዳም ዘር በሙሉ በኃጢአት ባርነት ተይዞ፣ ለ፶፻፭፻ ዓመታት በፍዳ አረንቋ ውስጥ ሲኖር ተስፋ ሲያደርግ የነበረው የእግዚአብሔር አብ ልጅ እግዚአብሔር ወልድ ለአዳም የገባለትን የመዳን ቃል ኪዳን ነው፡፡ ይህም ይፈጸም ዘንድ ነቢያት አስቀድሞ ትንቢት ተናግረዋል፡፡

ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስለ መወለዱ ፥ ወደ ግብፅ ስለ መሰደዱ ፥ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ ፥ ብርሃን በሆነው ትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ ፥ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለ መቀበሉና ስለ መሰቀሉ ፥ ስለ ትንሣኤው ፥ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፡፡

ነቢዩ ዳዊት “እጅህን ከአርያም ላክ አድነኝም” በማለት ሲማጸን (መዝ.፻፵፫፥፯) ነቢዩ ኢሳይያስ ደግሞ “እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች” በማለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም እንደሚወለድ አስቀድሞ ተናግሯል፡፡ (ኢሳ.፯፥፲፬) በዚህም የተስፋ ቃል “ኃይልህን አንሳ፤ እጅህንም ላክ” በማለት ነቢያት እየተማጸኑ ጾመዋል፡፡

የነቢያት ጾም (የገና ጾም) ከኅዳር ፲፭ ጀምሮ ለ ፵፫ ቀናት የሚጾም ሲሆን ፋሲካው (ፍቺው) በልደት በዓል ነው፤ ይህም ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳንና ምእመናን ጾመውታል፡፡ እኛም አምላካችን ቸርነቱን እንዲያበዛልን፣ ከፈተና እንዲያወጣን፣ ወቅታዊውን ሀገራዊ ችግር ይፈታልን ዘንድ፣ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ እንዲሠውረን ጾሙን እንጹም!

የጌታችን ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና የቅዱሳን ነቢያት ጸሎት፣ አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!

 

የሐዋርያት ጾም

ሐዋርያት ሙሽራው ክርስቶስ ከእነሱ በተለየ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸው መንፈስ ቅዱስን በተቀበሉ ማግስት ለአገልግሎታቸው መቃናት ትምህርታቸውን (ስብከታቸውን) በጾም ጀምረውታል፡፡ዛሬም እኛ ቅዱሳን ሐዋርያትን አብነት አድርገን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማግስት እነርሱ የጾሙትን ጾም እንጾመዋለን፡፡

“ሆሣዕና በአርያም” (ማቴ.፳፩፥፱)

ከደቀ መዛሙርቱም ሁለቱን ልኮ ቤተ ፋጌ ከምትባል ቦታ አህያ እና ውርንጫ አስመጥቶ በእነርሱም ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገባ። በዚያን ሰዓት ከይሁዳ አውራጃዎች ሁሉ የፋሲካን በዓል ለማክበር የተሰበሰቡት ሁሉ የኢየሱስን ወደ ኢየሩሳሌም መምጣት ሰምተው በእልልታ እና በዝማሬ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።” (ማቴ.፳፩፥፱)

“እርሱም በሌሊት ወደ ጌታችን ኢየሱስ መጣ” (ዮሐ.፫፥፩)

የዓለምን ኃጢአት አስወግዶ፣ ኃጢአተኞችን በፍቅሩ መረብ አጥምዶ፣ በቃሉ ትምህርት ልቡናቸውን ማርኮ፣ በተአምራቱ ኅሊናቸውን ገዝቶ የፈጠራቸውን ሰዎች ወደ ሕይወት መንገድ ሊጠራ የመጣው መሲሕ በአይሁድ ቤት እንደ ባላጋራ ይታይ ነበር። ከዚያም አልፎ የአይሁድ አለቆች የሥልጣናቸውን በትር ተጠቅመው፣ ቀጥቅጠው፣ ከእግራቸው በታች አድርገው ሊገዙት ይሹ ነበር። ተግሣፁን እና የተአምራቱን ኃይል በአዩ ጊዜም በቅንዓት ተነሳሥተው ሊወግሩት ምክንያት ይፈልጉ ነበር። የባሕርይ አምላክነቱን ገንዘቡ እንደሆነ ሲነግራቸው፣ ራሱንም የእግዚአብሔር ልጅ እያለ ሲጠራ ሲሰሙ የቅን ተቆርቋሪ መሳይ ጠባያቸው እስከ መግደል ድረስ እንዲደርሱ አድርጓቸዋል።

‹‹በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለው›› (ማቴ.፳፭፥፳፩)

በሰዎች ዘንድ መታመን መታደል ነው፤ እምነትን ጠብቆ መገኘት ደግሞ ታላቅነት ነው፡፡ መታመን የተሰጠን አደራ ጠብቆ መገኘት ለክብር ያበቃል፤ በሰውም ሆነ በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ መወደድንና መከበርን ያተርፋል፡፡ ለሰዎች ስንታመን እነርሱ ባያዩንም በሁሉ ቦታ ያለ፣ በቦታ የማይወሰን፣ በእርሱ ዘንድ ጨለማ የሌለበት እግዚአብሔር ያየናል፡፡ መታመናችን “ሰው አየን አላየን” ብለን ሳይሆን ለታመንንለት ነገር በፈቃዳችን መገዛት ስንችል፣ የታመነንን ስናከብር በምትኩ ለታላቅ ኃላፊነት እግዚአብሔር ይሾመናል (ይመርጠናል)፡፡

«በደብረ ዘይት ተቀምጦ አስተማረ» (ማር.፲፫፥፫)

በመዋዕለ ስብከቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ደቀ መዛሙርቱ የቤተ መቅደሱን ሥነ ሕንፃ በትኩረት እያንዳንዱን ነገር በመመልከት ሲያደንቁ እርሱ ግን ቤተ መቅደሱ እንደሚፈርስ፣ ከሞት በኋላ ተነሥቶ እንደሚያርግና ነገር ግን ዓለምን ለማሳለፍ ዳግም እንደሚመጣ ነገራቸው።

በሽተኛው ተፈወሰ!

ሕመም፣ በሽታና ክፉ ደዌ በሰዎች ሕይወት ውስጥ የሚያጋጥሙ የጤና እክሎች ናቸው፡፡ የሰው ዘር በሙሉ ከአዳም ጥፋት በኋላ ይህ ቅጣት እንደመጣበት ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡ አዳምና ሔዋን አትብሉ ተብሎ የነበረውን ዕፀ በለስ ከበሉ በኋላ ከደረሰባቸው መርገምት መካከል በሕመምና ሥቃይ እንዲቀጡ ነው፡፡ (ዘፍ.፫፥፲፮-፲፱)

ለምድራዊም ይሁን ለዘለዓለማዊው ሕይወታችን መገኘት፣ ድኅነትም ሆነ ፈውስ የሚገኘው በእግዚአብሔር አምላካችን ስናምንና ለእርሱ ስንታመን እንደሆነ ማወቅ ይገባል፡፡ መፃጉዕ ለጊዜው የተጠየቀው ነገር ከያዘው ደዌ እንዲድን ቢመስልም ጌታችን ግን የነፍሱንም ድኅነት ጠይቆታል፡፡ ‹‹ልትድን ትወዳለህን?›› ብሎ የጠየቀው ስለ እምነቱ ነበር፡፡ ከበሽታው ለመፈወስም እንኳን ቢሆን እምነት ከሌለ ሊድን እንደማይችል በቃሉ አስረድቶታል፡፡ ከዚያም አልፎ ተርፎ የነፍሱንም ነገር እንዲያስብ አሳስቦታል፡፡

“የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ” (ዮሐ.፪፥፲፮)

በቅዱስ ያሬድ ድጓ ውስጥ የምናገኘው ዐቢይ ጉዳይ አንጽሆ ቤተ መቅደስ ነው። “የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት” እንዲል። ይህ ብቻ አይደለም፤ ተቆጣቸው፤ ገሠጻቸው የሚሉ አስተማሪ ቃላቶችን አካቶ ይዟል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ይህንን በተመለከተ እንዲህ ይላል፡፡” በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ ርግብ ሻጪዎችንም። ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።” (ዮሐ.፪፥፲፬-፲፮)

“እግዚአብሔር ሰንበትን ቀደሳት፤ ከዕለታትም ከፍ ከፍ አደረጋት” (ጾመ ድጓ)

ቅዱስ ያሬድም ይህችን ቀን በጾመ ድጓው “ቀደሳ እግዚአብሔር ለሰንበት ወአልዓላ እምኩሉ ዕለት፤ እግዚአብሔር ሰንበትን ቀደሳት፤ ከዕለታትም ከፍ ከፍ አደረጋት” በማለት የቅድስት ሰንበትን ልዕልና በዜማ ያመሰግናታል። (ጾመ ድጓ ዘቅድስት ዘሰንበት)

ዘወረደ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ፤ አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አምላክ አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይ ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም”  እያለች በሰንበት ዋዜማ ዜማውን መሐትው (መግቢያ) አድርጋ የሳምንቱን ዜማ በማስተጋባት የጌታችንን ከሰማይ መውረድ ታመሠጥርበታለች፤ ታመሰግንበታለች። (ጾመ ድጓ፥ ዘዘወረደ ዋዜማ)