ወርኃ ጥር

በባሕረ ሐሳብ ቀመር መሠረት ቀኑ ዐሥር ሰዓት ሲሆን ከዚህ በኋላ ሌሊቱ እየጨመረ ይሄዳል። ጥር የሚለው ስያሜ “ጠር፣ ጠይሮ፣ ጠየረ፣ ጠሪእ፣ (ጠርአ፣ ይጠርእ፣ ጸርሐ) ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጒሙም “መጥራት፣ መጮኽ፣ አቤት ማለት” ነው፡፡ (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፭፻፲) ጥር የወር ስም ሆኖ በታኅሣሥ ወር እና በየካቲት ወር መካከል የሚገኝ፣ ከዐሥራ ሦስቱ ኢትዮጵያ የወራት አቆጣጠር ውስጥ አምስተኛው ነው።

በዚህም ወር ዘመነ አስተርእዮ ይታሰባል፤ አስተርእዮ በጥሬ ትርጉሙ “መገለጥ” ነው፤ ይህም ወቅት በዋናነት ስውር የነበረ ምሥጢረ ሥላሴ የተገለጠበት፣ ሰማያዊ አምላክ በኩነተ ሥጋ ለድኅነተ ዓለም ሲል በዚህ ዓለም የተገለጠበት፣ ሰማያዊ ምሥጢርም የታየበት ድንቅና ልዩ ዘመን ነውና እንዲህ ተብሎ ተጠራ።

‹‹ወልድ ተውህበ ለነ›› (ኢሳ.፱፥፮)

ውድ ክርስቲያኖች! ይህ የሰው ልጅ ታሪክ የተቀየረበትን ዕለት በደስታ፣ በፍቅር፣ የተጣላን ታርቀን፣ የበደልን ክሰን፣ በኃጢአት ያደፈ ሕይወታችን በንስሐ አንጽተን፣ በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ሕይወታችንን አስቀድሰን እናክብረው!

መልካም በዓል!

የሰው ተፈጥሮና ሥርዓተ ጾታ

የሰው ዘርና መሠረት የሆኑት አዳምና ሔዋን ስያሜያቸው በጾታ ተለይቶ በማይታይበት ሁኔታ (በጋራ ስያሜአቸው) ‹‹ሰው›› የሚሰኙ ሲሆን ‹‹አዳም›› በመባል የሚታወቀው ቀዳሚ ፍጥረትም ከወንድ ጾታ በተጨማሪ የሰው ዘር ሁሉ ምንጭና መጠረያ ሆኖም አገልግሏል፡፡

በአጠቃላይ ‹‹ተባዕታይ/ዊ/››- “ወንዳዊ፣ ወንድ፣ ወንዳማ፣ ወንዳ ወንድ፣ ብርቱም” ማለት ሲሆን ‹‹አንስታይ/ዊ/››- “ሴታም፣ ሴትማ፣ ሴት፣ ባለ ሴትም” የሚለውን ያመለክታል፡፡ አንስትና ብእሲት ለሰው ብቻ ይነገራል፡፡ (ዘፍ.፩፥፳፯)

ጾታቸውና ግብራቸው በአንድነት ሲገለጽ ደግሞ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ስያሜዎች የሚከተሉትን ትርጉሞች ይይዛሉ፡-

አዳም ማለት “የሚያምር፣ ደስ የሚያሰኝ ሰው፣ ደግ፣ መልከ መልካም፣ የመጀመሪያ ሰው፣ የሰው ሁሉ አባት” የሚል ትርጒም ተሰጥቶታል፡፡

ሔዋን ማለት “ሕይወት” ማለት ነው፡፡ “ሔዋን” ብሎ የሰየማትም አዳም ሲሆን ስያሜው ‹‹የሕያዋን ሁሉ እናት /እመ ሕያዋን/›› መሆኗን ያመለክታል፡፡ (ዘፍ.፪፥፬-፳፬) ከዚህም ሌላ ረዳት ትባላለች፡፡

የሰው ተፈጥሮና ሥርዓተ ጾታ

የሰው   ልጅ ተፈጥሮአዊ  ባሕርይ   በስሙ  ተገልጧል፡፡ የተለየ የሚያደርገውም በአምሳለ እግዚአብሔር  የተፈጠረ መሆኑ ነው፤ ነገር ግን አሁን ባለው ዓለም ውስጥ ክብሩን  ለማዋረድ  የሚሞክር  ነገረ  ህልውናም  ፍጹም  በተሳሳተ  እይታ  የሚተነትን  የሐሰት  “ሳይንስ” ይስተዋላል፡፡ መላእክት  ዕውቀት  አላቸው፤  ነገር  ግን  በኃይለ  ዘር አይራቡም:: ከዚህ በተቃራኒው  ደግሞ እንስሳት  ዕውቀት  የላቸውም፤ በኃይለ  ዘር ግን ይራባሉ፤  ሰው ግን እንደ መላእክት ዕውቀት  እንደ  እንስሳት ደግሞ በኃይለ  ዘር ስለሚራባ ከሁለቱም የተለየ ያደርገዋል፤  ዳግመኛም መላእክት  ሕያዋን  ናቸው፤  እንስሳት  ደግሞ  መዋትያን ናቸው፤  የሰው  ልጅ ግን  ሕያውም  መዋቲም  በመሆኑ የተለየ ነው፤ እግዚአብሔር  እንዲህ  ውብና ቅዱስ አድርጎ  የፈጠረው ስላለው ክብር ባለ መረዳትና ባለ ማወቁ ወደ ኃጢአት  ሲወድቅ  ይስተዋላል፡፡

ማኅበራዊ ሕይወታችን!

ሕይወታችንን ስናስብ የሌሎችን በሕይወት መቆየት እንጠባበቃለን። በጋራ ዓለም ላይ አብሮ የጋራ ዓለምን ማቅናት ላይ እንድንመረኮዝ እንገደዳለን። በሕገ ተፈጥሮ ውስጥ ለራሱ የተፈጠረ ፍጥረት የለም። ከእሑድ እስከ ዓርብ ያሉ ፍጥረታት እርስ በራሳቸው ተመጋጋቢ ቢሆኑም ሁሉም ግን ስለ አዳም ተፈጥረዋል። አንዳንዶቹ ለምግበ ሥጋ ምግበ ነፍስ፣ አንዳንዶቹ ለአንክሮ ለተዘክሮ፣ አንዳንዶቹ ለመድኃኒትነት፣ አንዳንዶቹ ለምስጋና፣ አንዳንዶቹ አዳም መሥዋዕት አድርጎ ሊያቀርባቸው፣ ሌሎቹ ደግሞ ለሌላ ለተለያየ ነገር ተፈጥረዋል። እነዚህ ሁሉ ለራሳቸው ሲባል አልተፈጠሩም።

ወርኃ ታኅሣሥ

ሰፊ አስተምህሮ እና ምሥጢር ካላቸው ወራት አንዱ የታኅሣሥ ወር ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ በባሕረ ሐሳብ ቀመር ቀኑ ዘጠኝ ሌሊቱ ዐሥራ አምስት ይሆናል፤ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጨመረ ሌሊቱ እያነስ ይሄዳል

የቅዱሳን አማላጅነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለጾመ ነቢያት (ለገና ጾም) አደረሳችሁ! ጾመ ነቢያት አባቶቻችን ነቢያት አምላካችን ተወልዶ ያድነን ዘንድ የጾሙት ጾም ነው፤ እኛ ደግሞ ከሰማያት ወርዶ፣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ አድኖናል ስንል ውለታውንና ፍቅሩን እያሰብን እንጾማለን!

በዘመናዊ ትምህርታችሁ የዓመቱን አንድ አራተኛ (ሩቡን የትምህርት ዘመን) ጨረሳችሁ አይደል! መቼም ከነበራችሁ ዕውቀት እንደጨመራችሁ ተስፋ እናደርጋለን! በርትታችሁ ተማሩ እሺ! መልካም!

ባለፈው ተከታታይ ትምህርታችን ስለ አማላጅነት ምንነት፣  ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ስለ ቅዱሳን መላእክት አማላጅነት በተወሰነ መልኩ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችንን አማላጅነት እንማራለን! ተከታተሉን!

ምድር እስከ መቼ ታለቅሳለች?

ምድር ዛሬ እያለቀሰች ነው፡፡ ግን እስከ መቼ ታለቅሳለች? ሰዎችስ ከክፋታቸው የሚመለሱት መቼ ነው? የምድረ በዳው ሣርስ እስከ መቼ ደርቆ ይቀጥላል? አዕዋፋትና እንስሳትስ እስከ መቼ ያልቃሉ? እግዚአብሔርስ ምድርን እስከ መቼ ነው የሚቆጣት? ቅዱሳንስ ስለ ደማቸው እስከ መቼ ምድርን ይካሰሷታል? ነቢዩ ኤርምያስ የሚጠይቀውን ጥያቄ አሁንም እኛ እንጠይቃለን፡፡

‹‹ሽማግሌዎች ከአደባባይ፥ ጎልማሳዎች ከበገናቸው ተሻሩ›› (ሰቆ.ኤር.፭፥፲፬)

በኤርምያስ ዘመን የሆነው እንዲህ ነበር፡፡ ልክ እንደ ዛሬው ክፉዎች ሠልጥነው ነበር፤ ከመከራቸው የተነሣ ልጆች፣ ድሃ አደጎችና አባት እናት የሌላቸው ሕፃናት ብዙዎች ነበሩ፤ እናቶች እንደ መበለቶች ሆነው ነበር፡፡ ውኃቸውን በብር እንጨቶቻቸውን፣ በዋጋ ገዝተው የተጠቀሙበት ጊዜ ነበር፡፡

‹‹ፈኑ እዴከ እምአርያም፤ ወአድኅነኒ፤ እጅህን ከአርያም ላክ፤ አድነኝም›› (መዝ. ፻፵፫፥፯)

ይህ ሱባኤ፣ ዘመነ ነቢያት፣ ወርኃ ጾመ ነቢያት ከመቼውም በላይ አስጨናቂዎቻችን፣ በሥጋ በነፍስ የሚዋጉን፣ አጋንንት ውሉደ አጋንንት፣ ረቂቃኑ አጋንንት፣ ልቡሰ ሥጋ አጋንንት፣ ሁሉ እንደ ጤዛ ረግፈው፣ እንደ ትቢያ ተበትነው፣ ከሕዝበ ክርስቲያንና ከቤተ ክርስቲያን ይርቁ ዘንድ፣ የክርስቶስም መንጋ በሰላም በበረቱ ያድር ዘንድ፣ ‹‹እጅህን ከአርያም ላክ፤ አድነንም››  የምንልበት ጊዜ ነው፡፡