ጽኑ እምነት

እለእስክንድሮስ የተባለው መፍቀሬ ጣዖት፣ ጸላዬ እግዚአብሔር፣ የዲያቢሎስ ምርኮኛ የሆነው በሰው እጅ ከድንጋይ ተጠርቦ ለተሠራው ጣዖት ሕዝቡን እንዲሰግዱ ሲያስገድድ፣ ስቶ ሲያስት፣ ሲያስፈራራ ኖሯል፡፡ አብዛኛው ለሥጋው ሳስቶ፣ መከራውን ተሰቆ ለጣዖት ሲሰግድ ሕፃን ቂርቆስ ግን እምቢ አለ፤ የቀደሙ አባቶቹን የተጋድሎ ታሪክ ያውቃልና ልቡን አጸና፤ ለመከራው ተዘጋጀ፤ እናቱ ለልጇ ሳስታ፣ ለጣዖት ልትንበረከክ፣ ልትክድ ሲዳዳት ሕፃኑ ግን ጸና፤ መከራውን ሳይሰቀቅ እለ እስከንድሮስ ላቆመው ጣዖት አልሰግድም አለ፡፡

‹‹አትጨነቁ…›› (ማቴ.፮፥፴፬)

ሰዎች  መልካምና ክፋ ነገርን ለማሳካት ይጨነቃሉ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹አትጨነቁ›› ያለን ለክፋትና ለኃላፊው ዓለም ተጨንቀን መፍትሔ ለማናመጣለት ነገር ነው፡፡ (ማቴ.፮፥፴፬) ፈጣሪያችን ለእኛ ለልጆቹ በዚህ ምድር በእንግድነት ስንኖር ምን እንደሚያስፈልገን ያውቃል፤ የሚያሻንንም ይሰጠናል፤ እናስብ ዘንድ አስተዋይ አእምሮ ሰጥቶናል፤ ማሰብ ከሚገባን በላይ ደግሞ ልንጨነቅ ስለማይገባ ‹‹አትጨነቁ›› አለ፡፡ አበው በብሂላቸው ‹‹…አስብ እንጂ አትጨነቅ..›› የሚሉን ለዚህ ነው፡፡ በምድር ስንኖር በማሰብ በመጠንቀቅ፣ በመጠበቅ እንደ ርግብ የዋህ እንደ እባብ ደግሞ ብልህ ሆነን ልንኖር ያስፈልጋል፡፡ ልንፈራና ልንጨነቅ እንደማይገባ ግን ክርስትናችን ያስተምረናል፡፡ ጌታችን ለአባቶቻችንን ቅዱሳን ሐዋርያት ስለሚቀበለው መከራ፣ ስለሞቱ ሲነግራቸው ባዘኑ ጊዜ ‹‹…ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም ደግሞ እመኑ…›› በማለት በአንዳች ነገር እንዳይጨነቁ ልባቸው እንዳይታወክ ነገራቸው፡፡ (ዮሐ. ፲፬፥፩)

ወርኃ ሐምሌ

ሐምሌ የወር ስም ሲሆን ሐምል “ሐመልማል” ከሚለው ግስ የተገኘ ነው፤ “ሐምል” ማለት “ቅጠል፣ ቅጠላ ቅጠል፣ ሣር፣ ቋያ፣ ቡቃያ፣ ተክል” ማለት ሲሆን ሐምሌ ማለት ደግሞ ቅጠላም ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፬፻፵፱)

ወሩ ስያሜውን ያገኘው ምድር የሰማይ ጠልን ስታገኝ በእርሷ ላይ ከሚታየው ተፈጥሮአዊ ለውጥ የተነሣ ነው፤ በበጋው ወራት ደርቃና ተሰነጣጥቃ የነበረች ምድር በክረምቱ መግቢያ የሚዘንበው ዝናብ ድርቀቷን አስወግዶ ሲያለሰልሳት ልምላሜ ይታይባታል፡፡ ሣሩ፣ ቅጠሉ በቅሎ በአረንጓዴ ዕፅዋት ተውባ የክረምቱን መግባት የበጋውን ማብቃት ታበሥርበታለች፡፡

ፍረጃና መዘዙ

ፍረጃ አንድን አካል ወይም ሰው ማንነቱን የማይገልጠው ስም፣ እውነታን ባላገናዘበ መልኩ ግላዊና ማኅበረሰባዊ በሆነ መንገድ ለሰዎች ስያሜ መስጠት ፣ ከአንድ ጉዳይ ተነሥቶ ሁሉን መጥላትና ማንቋሸሽ ነው፡፡ ፍረጃውን የሚያደርጉ ሰዎችም ፍረጃውን መሠረት አድርገው በክፉ የፈረጁት ግለሰብ ወይም ቡድን አንዳች ቅጣት እንዲደርስበት ስለሚፈልጉ ለዚያ ፍረጃና ቅጣት ምስክር አድርገው የሚያቀርቡት እውነታን ሳይሆን የራሳቸውን ትርክት ነው፡፡ ፍረጃ ሰዎችን ለማግለልና ለመነጠልም እንደ መሣሪያ ሆኖ የሚያገለግልና በቀላሉ የማይነቀልም ሂደት/ቀጣይነት ያለው ነው፡፡ ፍረጃውን ለሚያደርጉ ሰዎችና ፍረጃቸውንም ለሚቀበሉ ሰዎች በፈረጇቸው ሰዎች ላይ ከሕግና ከሥርዓት ወጥተው የራሳቸውን ፍርድ በመስጠት ከድብደባ እስከ ግድያ የሚደርስ ወንጀል እንዲፈጽሙ ያደርጋቸዋል፡፡

እግረ ኅሊና

ጉባኤ ዘርግተው በዐውድ ምሕረት ላይ በተመስጦ ቅዱስ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሲያስተምሩ የሰሚው በጎ ፈቃድና እዝነ ልቡና ከእነርሱ ጋር እንደሆነ በማመን ነው፡፡ የሕይወት ማዕድ ተዘጋጅቶ ሲቀርብም ታዳሚው ሊቋደስ የተገባ በመሆኑ በጆሮአችንም ሆነ በእዝነ ልቡናችን ሰምቶ መቀበል ድርሻችን ነው፡

“መባዬን በመያዝ ወደ ቤትህ እገባለሁ” (መዝ.፷፭፥፲፫)

ድንቅ በሆነ ሥራው ዓለምን ከእነ ጓዟ ለፈጠረ አምላክ የሚበቃ ከሰው ዘንድ የሚሰጥ ምን ነገር ይኖራል? ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ባለ ጸጋው አምላካችን ልናቀርብስ የምንችለው ከእኛ የሆነ ከእርሱ ዘንድ ዋጋ ያለውስ ነገር ምን ይሆን? እርሱ ባወቀና በፈቀደ ከእርሱ የሆነ ግን ከእኛ የሚሰጥ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ስጦታን እንድናቀርብ ግን ተሰጠን፡፡ “ለከበረ ስምህም ከአንተ የተገኘውን ዕጣን አቀረብንልህ” እንዲል፡፡ ሁሉ በእጁ ለሆነው አምላክ ስጦታ እንድናቀርብም ክቡር ፈቃዱ ሆነልን፡፡

የተቀደሰ ውኃ

“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ። ምድርም ባዶ ነበረች፥ አንዳችም አልነበረባትም፤ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር።” (ዘፍ.፩፥፩-፪)

የሐዋርያት ጾም

ሐዋርያት ሙሽራው ክርስቶስ ከእነሱ በተለየ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸው መንፈስ ቅዱስን በተቀበሉ ማግስት ለአገልግሎታቸው መቃናት ትምህርታቸውን (ስብከታቸውን) በጾም ጀምረውታል፡፡ዛሬም እኛ ቅዱሳን ሐዋርያትን አብነት አድርገን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማግስት እነርሱ የጾሙትን ጾም እንጾመዋለን፡፡

ርደተ መንፈስ ቅዱስ

በዓለ ጰራቅሊጦስ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ፣ የቤተ ክርስቲያንን ልደትና የሐዋርያትን ለወንጌል አገልግሎት መታጠቅ የምናስብበት ታላቅና ቅዱስ በዓል ነው።

ወርኃ ሰኔ

ወርኃ ሰኔ በዓመት ውስጥ ከሚገኙ ዐሥራ ሦስት ወራቶች መካከል ዐሥረኛው ወር ነው፤ ስለ ቃሉ ትርጒም መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ ጀምረው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ፈጽመውት ደስታ ተክለ ወልድ ባሳተሙት መዝገበ ቃላት መጽሐፍ ላይ “ሰነየ” ከሚለው ግስ የተገኘ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ሰኔ ማለትም “ሰነየ፣ አማረ፣ መሰነይ፣ ሁለት ማድረግ፣ ማጠፍ ፣መደረብ፣ በመልክ በባሕርይ መለወጥ፣ ሌላ መሆን፣ መምሰል” እያለ ይተረጉመዋል፡፡ (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፸፭)