‹‹የማይመረመር ብርሃን!›› (ሥርዓተ ቅዳሴ)
የማይመረመረው ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳኑ ምሥጢር ከፍጥረት ረቂቅ (የማይመረመር) ነው፡፡ በመስቀል ላይ ሁኖ አምላክነቱን በገለጸ ጊዜ ጠላት ዲያብሎስ እንዲህ ብሏል፤ ‹‹… ያለኃጢአት የሞተ ይህ ማን ነው? በብርሃኑ ብዛት የጨለማውን አበጋዝ ዕውር ያደረገው ይህ ማን ነው?›› (ሃይማኖተ አበው ትምህርት ኅቡዓት ፬፥፲፮)
የማይመረመረው ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳኑ ምሥጢር ከፍጥረት ረቂቅ (የማይመረመር) ነው፡፡ በመስቀል ላይ ሁኖ አምላክነቱን በገለጸ ጊዜ ጠላት ዲያብሎስ እንዲህ ብሏል፤ ‹‹… ያለኃጢአት የሞተ ይህ ማን ነው? በብርሃኑ ብዛት የጨለማውን አበጋዝ ዕውር ያደረገው ይህ ማን ነው?›› (ሃይማኖተ አበው ትምህርት ኅቡዓት ፬፥፲፮)
እውነተኛው የወይን ግንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን ይፈጽም፣ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል መፀነሡን ያበስር ዘንድ ወደ እመቤታችን በተላከ ጊዜ የተነገረ ቃል ነው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ብሥራትን ይናገር ዘንድ ወደ እመቤታችን በተላከ ጊዜ በግንባሩ ተደፍቶ ልዑል እግዚአብሔርን ‹‹ጌታ ሆይ! የምትነግረኝ ይደረግ ዘንድ እንደምን ይሆናል?›› አለው፡፡ ጌታም ‹‹የጀመርኩትን ቸርነት ፈጸምኩ፣ የወይን ግንድ ይቆረጣል፤ ወይራም ከበለስ ጋር ይተከላል፤ ቅጽሮችም ይቀጸራሉ (ምግባር ከሃይማኖት ጋር ይሠራል)፤ ገብርኤል ሆይ! ሄደህ ለዳዊት ልጅ ‹‹እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ›› ብለህ አብሥራት›› አለው፡፡ ‹‹ለዘለዓለም ነግሦ የሚኖረውን እነሆ ትፀንሳለሽ በላት›› አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ሰገደ፡፡ ጌታችን ‹‹እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ›› በማለት እንደተናገረው የወይን ግንድ የተባለ እርሱ ነው፡፡ (ዮሐ.፲፭÷፩)
ከደቀ መዛሙርቱም ሁለቱን ልኮ ቤተ ፋጌ ከምትባል ቦታ አህያ እና ውርንጫ አስመጥቶ በእነርሱም ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገባ። በዚያን ሰዓት ከይሁዳ አውራጃዎች ሁሉ የፋሲካን በዓል ለማክበር የተሰበሰቡት ሁሉ የኢየሱስን ወደ ኢየሩሳሌም መምጣት ሰምተው በእልልታ እና በዝማሬ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።” (ማቴ.፳፩፥፱)
የዓለምን ኃጢአት አስወግዶ፣ ኃጢአተኞችን በፍቅሩ መረብ አጥምዶ፣ በቃሉ ትምህርት ልቡናቸውን ማርኮ፣ በተአምራቱ ኅሊናቸውን ገዝቶ የፈጠራቸውን ሰዎች ወደ ሕይወት መንገድ ሊጠራ የመጣው መሲሕ በአይሁድ ቤት እንደ ባላጋራ ይታይ ነበር። ከዚያም አልፎ የአይሁድ አለቆች የሥልጣናቸውን በትር ተጠቅመው፣ ቀጥቅጠው፣ ከእግራቸው በታች አድርገው ሊገዙት ይሹ ነበር። ተግሣፁን እና የተአምራቱን ኃይል በአዩ ጊዜም በቅንዓት ተነሳሥተው ሊወግሩት ምክንያት ይፈልጉ ነበር። የባሕርይ አምላክነቱን ገንዘቡ እንደሆነ ሲነግራቸው፣ ራሱንም የእግዚአብሔር ልጅ እያለ ሲጠራ ሲሰሙ የቅን ተቆርቋሪ መሳይ ጠባያቸው እስከ መግደል ድረስ እንዲደርሱ አድርጓቸዋል።
በሰዎች ዘንድ መታመን መታደል ነው፤ እምነትን ጠብቆ መገኘት ደግሞ ታላቅነት ነው፡፡ መታመን የተሰጠን አደራ ጠብቆ መገኘት ለክብር ያበቃል፤ በሰውም ሆነ በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ መወደድንና መከበርን ያተርፋል፡፡ ለሰዎች ስንታመን እነርሱ ባያዩንም በሁሉ ቦታ ያለ፣ በቦታ የማይወሰን፣ በእርሱ ዘንድ ጨለማ የሌለበት እግዚአብሔር ያየናል፡፡ መታመናችን “ሰው አየን አላየን” ብለን ሳይሆን ለታመንንለት ነገር በፈቃዳችን መገዛት ስንችል፣ የታመነንን ስናከብር በምትኩ ለታላቅ ኃላፊነት እግዚአብሔር ይሾመናል (ይመርጠናል)፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ዐቢይ ጾም (ጾመ ክርስቶስ) አምስተኛው ሳምንት ላይ እንገኛለን፤ በአቅማችሁ በመጾም በጸሎት እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው፤ በሰንበት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ማስቀደስና መንፈሳዊ ትምህርትን ከመማርም መዘንጋት የለብንም!
በእግዚአብሔር ቤት ስናድግ እንባረካለን፤ አምላካችንም ጥበቡንና ማስተዋሉን ያድለናል፤ በጥሩ ሥነ ምግባር አድገን፣ ለራሳችን ለቤተሰቦቻችን እንዲሁም ለአገራችን መልካም የምንሠራም እንሆናለን፡፡ በዘመናዊ ትምህርታችሁም በርትታችሁ መማር ይገባል፡፡ የሁለተኛ መንፈቀ ዓመት እየተገባደደ ነውና በርትታችሁ ትማሩ ዘንድ አጥኑ፤ ያልገባችሁን ጠይቁ፤ አብዛኛውን ጊዜያችሁን በትምህርታችሁ አተኩሩ፡፡ መልካም! በዛሬው ትምህርታችን ሐሰት (ውሸት) በሚል ርእስ እንማራለን፡፡
በመዋዕለ ስብከቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ደቀ መዛሙርቱ የቤተ መቅደሱን ሥነ ሕንፃ በትኩረት እያንዳንዱን ነገር በመመልከት ሲያደንቁ እርሱ ግን ቤተ መቅደሱ እንደሚፈርስ፣ ከሞት በኋላ ተነሥቶ እንደሚያርግና ነገር ግን ዓለምን ለማሳለፍ ዳግም እንደሚመጣ ነገራቸው።
ከአበው አንዱ “እግዚአብሔርን የማስደስተው ምን ባደርግ ነው? በጾም ነው? ወይስ በድካም ነው? ወይስ በምሕረት? ወይስ በትጋህ?” ብሎ ለጠየቀው ወንድም “አዎ፤ በእነዚህ ግብራት እግዚአብሔርን ደስ ልታሰኘው ትችላለህ። ነፍሳቸውንና ሥጋቸውን ያለ ዕረፍት ያደከሙ ብዙዎች እንደ ሆኑና ድካማቸው ግን ከንቱ እንደ ሆነ በእውነት እነግርሃለሁ። አፋችን መዓዛው እስኪለወጥ ድረስ አብዝተን ጾምን፣ የመጻሕፍትን ቃልም አጠናን፣ እግዚአብሔር የሚወደውን ፍቅርንና ትሕትናን ግን ገንዘብ አላደረግንም” በማለት ነበር የመለሰለት። ስለዚህ ለሁሉም መንፈሳዊ ተጋድሎዎችም ትጥቆችም መሠረትም ፍጻሜም ናት። ፍቅርንና ትሕትናን ገንዘብ በማድረግ ንጽሕ ጠባይዕን ገንዘብ ማድረግ የክርስትና ሕይወት መሠረት ነው። (ከበረሃውያን ሕይወትና አንደበት በመምህር ያረጋል አበጋዝ)
በመጋቢት ወር በኢትዮጵያ ዘንድ መዓልቱ እየጨመረ ሌሊቱ እያጠረ የሚሄድ ሲሆን የመዓልቱ ርዝመት ፲፪ ሰዓት የሌሊቱም ፲፪ ሰዓት ይሆናል። በክፍል በሚቆጥረው በሄኖክ አቆጣጠር ደግሞ የመጋቢት ወር መዓልቱ ዘጠኝ ክፍል ሌሊቱም ዘጠኝ ክፍል እኩል ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ሰባተኛው ወር ወርኀ መጋቢት ይባላል። መጋቢት በቁሙ “ስመ ወርኅ፣ ሳብዕት እመስከረም፣ የመዓልትና የሌሊት ምግብና ትክክል የሚሆንበት ወርኅ ዕሪና” ማለት ነው። “እስመ ይዔሪ መዓልተ ወሌሊተ አመ እስራ ወኀሙሱ ለወርኀ መጋቢት፤ በመጋቢት ወር ፳፭ ቀን ሌሊቱና መዓልቱ ይስተካከላልና” እንዲል፡፡ (ዲድስቅልያ ፴፣ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፭፻፸፯)