የተቀደሰ ውኃ
“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ። ምድርም ባዶ ነበረች፥ አንዳችም አልነበረባትም፤ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር።” (ዘፍ.፩፥፩-፪)
“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ። ምድርም ባዶ ነበረች፥ አንዳችም አልነበረባትም፤ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር።” (ዘፍ.፩፥፩-፪)
ሐዋርያት ሙሽራው ክርስቶስ ከእነሱ በተለየ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸው መንፈስ ቅዱስን በተቀበሉ ማግስት ለአገልግሎታቸው መቃናት ትምህርታቸውን (ስብከታቸውን) በጾም ጀምረውታል፡፡ዛሬም እኛ ቅዱሳን ሐዋርያትን አብነት አድርገን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማግስት እነርሱ የጾሙትን ጾም እንጾመዋለን፡፡
በዓለ ጰራቅሊጦስ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ፣ የቤተ ክርስቲያንን ልደትና የሐዋርያትን ለወንጌል አገልግሎት መታጠቅ የምናስብበት ታላቅና ቅዱስ በዓል ነው።
ወርኃ ሰኔ በዓመት ውስጥ ከሚገኙ ዐሥራ ሦስት ወራቶች መካከል ዐሥረኛው ወር ነው፤ ስለ ቃሉ ትርጒም መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ ጀምረው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ፈጽመውት ደስታ ተክለ ወልድ ባሳተሙት መዝገበ ቃላት መጽሐፍ ላይ “ሰነየ” ከሚለው ግስ የተገኘ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ሰኔ ማለትም “ሰነየ፣ አማረ፣ መሰነይ፣ ሁለት ማድረግ፣ ማጠፍ ፣መደረብ፣ በመልክ በባሕርይ መለወጥ፣ ሌላ መሆን፣ መምሰል” እያለ ይተረጉመዋል፡፡ (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፸፭)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ እንዲሁም ለበዓለ ኀምሳ አደረሳችሁ! ለአባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የወረደበትን በዓለ ኀምሣ ባከበርን ማግስት ጾመ ሐዋርያት ይገባል፡፡ አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን ከተቀበሉ በኋላ ጥበብ ማስተዋሉን አግኝተው በእምነት ጸንተው የምሥራቹን ወንጌል ለማስተማር ከመሄዳቸው በፊት ጾምን ጾመዋል፡፡ ይህን ጾም ሁል ጊዜ ከበዓለ ኀምሳ ማግሥት ጀምሮ እስከ ሐምሌ አምስት ድረስ እንጾመዋለን፡፡
በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዐዋጅ ከሚጾሙ ሰባቱ አጽዋማት አንዱ ይህ ጾመ ሐዋርያት ወይም በተለምዶ የሰኔ ጾም እየተባለ የሚጠራው ነው፤ እኛም በአቅማችን ይህንን ጾም ልንጾም ይገባናል፤ ከአባቶቻችንን ቅዱሳን ሐዋርያት በረከትን ለማግኘት፣ ጾሙን እንጽም፤ በዘመናዊ ትምህርታችን ትምህርት ጨርሰን የማጠቃለያ ፈተና የምንፈተንበት ወቅት ነውና በርትተን እናጥና ፤ በመጪው ክረምትም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመገኘት መንፈሳዊ ትምህርትን ለመማር ከአሁኑ እናቅድ (እንዘጋጅ) መልካም! ውድ ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለ “ምጽዋት” ነው፡፡
የበዓለ ዕርገት ታሪካዊ አመጣጥ ከራሱ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ ጋር የተያያዘ ነው። ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያቱ ለአርባ ቀናት እየተገለጸ፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት አስተምሯቸዋል። (ግብረ ሐዋርያት ፩፥፫) እነዚህ አርባ ቀናት ሐዋርያት ትንሣኤውን እንዲያረጋግጡና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያውቁ ያደረገባቸው ጊዜያት ነበሩ።
አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም በግንቦት ሃያ አንድ ቀን ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ።
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በዓለ ኀምሳን እንዴት አያሳለፋችሁ ነው? በዓለ ዕርገትም እየደረሰ ነውና በዓሉን ለማክበር መዘጋጀት ያስፈልጋል! ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከማረጉ በፊት በተለያየ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት እየተገለጠላቸው ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ያስተምራቸው ነበር፡፡ በዚህም መሠረት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስናገለግል በሥርዓት ነው፡፡ በትምህርታችንም መበርታት እንዳለብን እንረዳለን፡፡ የፈተና ወቅት እየደረሰ በመሆኑ ከዚያ በፊት በርትተን በማጥናት ዕውቀት አግኝተን ከክፍል ወደ ቀጣይ ክፍል በጥሩ ውጤት መሸጋገር ይገባናል፤ መልካም ልጆች! ለዛሬ ስለ ተስፋ መንግሥተ ሰማያት እንማራለን፡፡
በዚህ ዓለም ያለ ደስታ ሁሉ ተለዋዋጭ ነው፡፡ መውደቅ መነሣት፣ ማዘን መደሰት ያለ ነው፡፡ ገንዘብ ያገኘ ይደሰታል፤ ሲያጣ ያዝናል፤ ምድራዊ ኑሮ ተለዋዋጭ ነው፤ ጊዜም ይመላለሳል፤ ይመሻል፤ ይነጋል፤ ምድር ላይ ቋሚ ነገር የለም። ደስታ ግን ለእግዚአብሔር ለተገዙት እንደ ሕጉ ለሚኖሩት ግን አብራ ትኖራለች፡፡
ሊቁ ደራሲ በተለወደ በ፸፭ ዓመቱ በሰሜን ተራራ ውስጥ ደብረ ሐዊ ከሚባል ገዳም ግንቦት ፲፩ ቀን የተሠወረ እንጂ የሞተ አይደለም፡፡ እርሱንና ሥራዎቹንም በየዓመቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትዘክራለች፡፡ የዝማሬና መዋሥዕት መምህራን የቅዱስ ያሬድን ጉባኤ ተክተው አሁንም ድረስ በማስተማር ላይ ናቸው፡፡