ዘወረደ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ፤ አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አምላክ አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይ ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም”  እያለች በሰንበት ዋዜማ ዜማውን መሐትው (መግቢያ) አድርጋ የሳምንቱን ዜማ በማስተጋባት የጌታችንን ከሰማይ መውረድ ታመሠጥርበታለች፤ ታመሰግንበታለች። (ጾመ ድጓ፥ ዘዘወረደ ዋዜማ)

“የጠገበች ነፍስ የማር ወላላ ትረግጣለች፤ ለተራበች ነፍስ ግን የመረረ ነገር ሁሉ ይጣፍጣታል።” (ምሳሌ ፳፯፥፯)

ንጉሥ ሰሎሞን የሰው ልጅ በጥጋብ ሲኖር ፈጣሪው እግዚአብሔርንም እንኳን እንደሚረሳ “የጠገበች ነፍስ የማር ወለላ ትረግጣለች” እያለ የጥበብ ቃልን ተናገረ። ለፈቃድ መገዛት እና ሆዳምነት ጠቢቡ እንደተናገረ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ተደጋግሞ ሲነገር በሊቃውንት አበው በተስፋ ተገልጧል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዮሐንስ ወንጌልን በተረጎመበት ፵፭ኛ ድርሳኑ ሆዳምነት የሰው ልጆችን ወደ ዲያብሎስ መንገድ የሚወስድ የጥፋት ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነ ይነግረናል። “ከሆዳምነት በላይ የከፋ እና አዋራጅ ምንም ነገር የለም። አእምሮን ያፈዛል፣ ነፍስን በጠፊ ሐሳብ ያስራል፣ የያዛቸውንም ሰዎች አውሮ እንዳያዩ ያግዳቸዋል።” [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ትርጓሜ ወንጌለ ዮሐንስ፣ ድርሳን ፵፭]

“ስለ ምን ጾምን?” (ኢሳ.፶፰፥፫)

የነነዌ ከተማ ሰዎች ኃጢአት በትንቢተ ዮናስ ውስጥ አንድ ሁለት ተብሎ አልተገለጸም፤ በጥቅሉ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ” ተብሎ በእግዚአብሔር ከመገለጹ በቀር አልተዘረዘረም። (ዮናስ ፩፥፪) ሆኖም ክፉታቸው ወደ ፊቴ ወጥቶአልና የሚለው የልዑል አምላክ ቃል የኃጢአታቸውን ታላቅነት ያመለክታል። ኃጢአታቸው በዮናስ መጽሐፍ ውስጥ አልተዘረዘረም አልን እንጂ በሌሎቹ መጻሕፍት ውስጥ ግን ተዘርዝሯል። ለምሳሌ ነቢዩ ናሆም የነነዌ ኃጢአት ምን ምን እንደነበረ ገልጿል። እነዚህም፡-

ወርኃ የካቲት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ስድስተኛው ወር “የካቲት” ተብሎ ይታወቃል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል “ከተተ” ከሚለው ግስ ከወጣው “ከቲት፣ ከቲቶት” ከሚል ንኡስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን በቁሙ “የወር ስም፣ ስድስተኛ ወር፣ የመከር ጫፍ (መካተቻ)፣ የበልግ መባቻ ማለት ነው” ብለው ተርጉመውታል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፭፻፲፭)

ሌሎችም ጸሐፍያን “የካቲት” የሚለው ቃል “ከቲት፣ ከቲቶት” ከሚል የግእዝ ንኡስ አንቀጽ የተገኘ ሲሆን “መውቃት፣ ማምረት፣ መሰብሰብ፣ መክተት” የሚል ትርጉም ይኖረዋል ካሉ በኋላ ይህንም ስም ያገኘው የካቲት ወር አዝመራ (ምርት) ወደ ጎተራ የሚከተትበት ወራት በመሆኑ ነው ብለዋል። (ኅብረ ኢትዮጵያ፣ ከቴዎድሮስ በየነ፣ አዲስ አበባ ፲፱፻፺፱ ዓ.ም፡፡ አንድሮ ሜዳ፣ ገጽ ፫፻፺፭፣ አቡሻክር የጊዜ ቀመር፣ በኢንጅነር አብርሃም አብደላ ገጽ ፵፱) በቁጥር ትምህርት አንዱ ወር በባተበት የትኛው ወር እንደሚብት በቃል የሚጠና ሲሆን የካቲት በባተችበትም ጳጕሜን እንዲሁም የካቲት በባተበት ሳኒታ ሰኔ ይብታል፡፡

‹‹እግዚአብሔር ፍቅር ነው›› (፩ኛ ዮሐ.፫፥፱)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ አጋማሽ ፈተናስ እንዴት ነበር? መቼም በርትቶ ሲማርና ሲያጠና ለነበረ ተማሪ ፈተናው እንደሚቀለው ተስፋ አለን፤ ጎበዝ ተማሪ የሚያጠናው ፈተና ሲደርስ ብቻ አይደለምና! መምህራን ሲያስተምሩ ተግቶ በአግባቡ የሚከታተል ያልገባውን የሚጠይቅ፣ መጻሕፍትን የሚያነብ የበለጠ ዕውቀት ለማግኘት ተግቶ የሚያጠና ነው!

ታዲያ እንደዚህ አድርጎ ትምህርቱን የሚከታተል ጥሩ ውጤትን ያመጣል! እንግዲህ በተለያየ ምክንያት በግማሽ ዓመቱ ፈተና በደንብ ያልሠራችሁ በቀሪው የትምህርት ዘመን በርትታችሁ በማጥናት ዕውቀትን እንድታገኙና ጥሩ ውጤት እንድታመጡ አደራ እንላለን!

ልጆች! ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁም ጎበዞች መሆን አለባችሁ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ተማሩ! መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ‹‹ተስፋ››  በሚል ርእስ  ስለ ተስፋ ተምረናል፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ፍቅር እንማራለን!

‹‹ምድር በውስጧ የሚኖሩትን ታስደነግጣቸዋለች›› (ዕዝራ ሱቱኤል ፬፥፳፬)

ዛሬ የምድር መሠረቶች እየተናወጡ ነው፡፡ ሕይወት ያለውን ፍጡር ሁሉ መድረሻና ጥግ ያሳጣ ፈተና በምድር ላይ እየታየ ነው፡፡ ምድር እንደ ዛፍ የምትወዛወዝበት፣ እሳት የምትተፋበት፣ ሊቆሙባት፣ ሊተኙባት የምታስጨንቅና የምታስደነግጥ ሆናለች፡፡ ይህም በሰው ልጆች ዓለም ውስጥ አስጨናቂው ጊዜ ነው፡፡ ሰዎች ከፍተዋል፤ ተፈጥሮም ከፍታለች፤ ሰዎች ፈጣሪንና ተፈጥሮን በድለዋል፤ እግዚአብሔርና ተፈጥሮ ደግሞ የቁጣቸውን ጅራፍ አንሥተዋል፡፡ ይህም የዘመኑ ፍጻሜ ስለመድረሱ አመላካችም እንደሆነ መልአኩ እንዲህ ሲል ነግሮታል፡፡ ‹‹ተነሥተህ በእግርህ ቁም፤ ጩኸት የተሞላበትን ቃል እነግርሃለሁ፡፡ መነዋወጥ አንተ የቆምህበት ቦታ ቢነዋወጽ መነዋወጹ የኅልፈት ምልክት ነውና፡፡ ያን ጊዜ የምድር መሠረቶች የኅልፈትን ምልክት ያስረዳሉ›› በማለት፡፡ (ዕዝ.፬፥፲፬)

ጋብቻና ጾታ

ፈቃድ ለሐሳብ መነሻ ነው፤ አንድ ሰው አንድን ጉዳይ ማሰብ የሚጀምረው ከፈቃዱ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ሐሳብና ፈቃድ በአገባባዊ ፍቺአቸው ተለዋዋጭና ተመሳሳይ የሚተካካ ትርጒም ይኖራቸዋል፡፡ ጋብቻም በጥሬ ትርጉሙ ኪዳን ማለት በመሆኑ በሁለት አካላት መካከል የሚፈጸም ውል ስምምነት ነው፡፡ አንድን ጎጆ ለመምራት በፈቃድ ላይ የሚመሠረት ውል (ኪዳን) ነውና፤ የጋብቻ ኪዳን በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን መጨረሻው ደግሞ ይህ ዓለም ሳይሆን ተስፋ የምናደርጋት መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡

የጥምቀት በዓል

አሁን ግን ‹‹መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ›› እንዲል (፩ኛ ጴጥ.፪፥፭) ከኃጢአት ርቀን፣ በቅንነት፣ በእምነት፣ በበጎ ሕሊና እንድንመላለስ ከብርሃነ ከጥምቀት ጸጋና በረከት እንድናገኝ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን።

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!

፲፫፻፹፮ አዳዲስ አማንያን የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን ማግኘታቸው ተገለጸ!

በደቡብ ኦሞ እና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ዳሰነች ወረዳ ፲፫፻፹፮ አዳዲስ አማንያን በማኅበረ ቅዱሳን የሐዋርያዊ ተልእኮ አስተባባሪነት የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን ማግኘታቸው የተገለጸ ሲሆን ተጠማቂያኑ ባለፉት ወራት መሠረታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት ሲማሩ  ከነበሩ ወገኖች መካከል  መሆናቸው ታውቋል፡፡ ሥርዓተ ጥምቀታቸውም በኦሞ ብሔረ ብፁዓን አቡነ ዜና ማርቆስ ወአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  አንድነት ገዳም ጥር ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ተፈጽሟል።