አገልግሎቴን አከብራለሁ!

በ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. ማኅበረ ቅዱሳን ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናትና ምርምር ማእከል›› በመክፈት ቅዱሳት መጻሕፍትን ማስተዋወቅ እና ከሚደርስባቸው ልዩ ልዩ ጉዳዮች አደጋዎች ተጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላላፉ ማድረግ ያቋቋመው የአገልግሎት ክፍል ለዛሬው የጥናትና ምርምር ማእከል መመሥረት ምክንያት ነው። ይህ ክፍል በተሻለ አደረጃጀትና የሰው ኃይል ተጠናክሮ ከኅዳር ወር ፳፻፩ ዓ.ም. ጀምሮ ‹‹የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል›› በሚል ስያሜ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

አገልግሎቴን አከብራለሁ!

አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህር ቤት ከተመሠረተበት ከ ፲፱፻፺፭ ዓ.ም. እስከ ፳፻፮ ዓ.ም. በባለቤትነት የአስተዳድረው የነበረው ማኅበረ ቅዱሳን ነበር፡፡ ከአገልግሎቱ እና መዋቅራዊ አደረጃጀት ባሕርይው አንጻር ሁለት መሠረታዊ ተግዳሮቶች ሲፈትኑት ቆይተዋል፡፡ የመጀመሪያው ለትምህርት ቤት የሚሆን የራሱ የሆነ ሕንፃ አለመኖር ሲሆን ሁለተኛው የሚፈለገውን የትምህርት ጥራት ለማምጣት የሚያስችሉ ግብዓቶችን ለማሟላት የሚያስችል የገንዘብ አቅም ማነስ ነው፡፡ ይህንን ችግር በዘለቄታው ለመፍታት ይቻል ዘንድ ማኅበረ ቅዱሳን፣ አባላቱ፣ የተማሪዎች ወላጆች እና የዓላማው ደጋፊዎች የሆኑ ግለሰቦች በጋራ ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማኅበር (ኤስድሮስ በ፲፰ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአንድምታ ትርጓሜ መምህር የነበሩ ናቸው) በማቋቋም ከሐምሌ ወር ፳፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ የባለቤትነት ዝውውር ተደረገ፡፡ (የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መተዳደሪያ ደንብ)

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ፳፻፲፯ ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት ዐዋጅ መግለጫ

‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ ጉባኤውንም ዐውጁ፤ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ።›› (ኢዩ.፩÷፲፬)

የቱን ታስታውሳላችሁ? የጥያቄዎቹ ምላሾች

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ! ነቢያት በብሉይ ኪዳን “አቤቱ ከሰማያት ወርደህ፣ ተወልደህ አድነን” ብለው የተነበዩት ትንቢት ተፈጽሞ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደበትን ቀን በድምቀት እናከብር ዘንድ ይገባል፡፡

ልጆች! ለዛሬ “የቱን ታስታውሳላችሁ?” በሚለው ላቀረብንላችሁ ጥያቄዎች ምላሾቹን ይዘን ቀርበናል፡፡ አንብባችሁ ምላሽ የሰጣችሁ በርቱ! ያልመለሳችሁ ደግሞ በቀጣይ በምናዘጋጀው ጥያቄና መልስ ተሳተፉ!

መልካም እረኛ!

“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና።”

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ አምስት ቁጥር ፻፷፬ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት ፲፩ እስከ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

የአቋም መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ፵፫ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ የአቋም መግለጫ

በወቅታዊ ጉዳዮች ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

ቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ጸዋትወ መከራን፣ ሞትንና ስደትን፣ የመቀበል ታሪኳ ዛሬ የተጀመረ ባይሆንም በአሁኑ ጊዜ የሰው ልጅ ይሀረንና መሰል መተኪያ የሌለው ሕይወት የሚያጠፋና ሥጋት ላይ የሚጥሉ ተፈጥሮአዊ፣ ሰብአዊ ክብሩን የሚያራክስ ተግባራት እንዳይደገሙ ለማድረግ በሚጥርበት ዓለም ችግሩ በተለይም በሀገራችን እየተባባሰ መቀጠሉ እጅግ ያሳስበናል፡፡