ጌታችን ፈዋሽ ውኃን አፈለቀ!

ሰኔ ስምንት ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው:: እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው::

ቃና ዘገሊላ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ሙሽራ አጊጣ፣ ለበጉ ሰርግ ያለ እድፍና ያለ ነውር ውብ ሆና ተዘጋጅታ በምትቀርብበት በዚያ ሰማያዊ ሰርግ ለመገኘትና ወደ በጉ ሰርግ ራት ገብተን፣ ካጌጡ ቅዱሳን ጋር ለመቀመጥና ለመብላት የበቃን ያድርገን፡፡

መልካም እረኛ!

“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና።”

ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ

የአባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ተጋድሎ በጽኑ መሠረት ላይ በመገንባቱ የመከራ ዝናብ ቢዘንብ፣ የሥቃይ ጎርፍ ቢጎርፍ፣ የችግር ነፋስ ቢነፍስ አይወድቅም፡፡ (ማቴ.፯፥፳፭) ይህም የሆነው እነርሱን በመንፈሳዊ ሕይወት የተተከለ፣ በተጋድሎ ያሳደገ፣ ገቢረ ተአምራት ወመንክራት በማድረግ እንዲያብቡ ያደረገና ለፍሬ ክብር ያበቃ የክብር ባለቤት አምላካችንና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ ነው፡፡

“በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን ?” (ሐዋ.፰፥፴)

ብዙዎች ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ወጥተው የቀሩት የመጽሐፍ ቅዱስን ንባብ እንዲሁ በፈቃዳቸው እና በግል ምልከታቸው ለመተርጎም በሚያረጉት ሙከራ ነው። ቤተ ክርስቲያን ግን እንደ ሠለስቱ ምዕት፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ አትናቴዎስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮስ፣ ቅዱስ ቄርሎስ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን የመሳሰሉ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የጻፏቸውን ድርሳናትና ትርጓሜያት ለልጆቿ በማስተማር ከግል አረዳድ ወጥተን የተነገረበትን ትክክለኛ ዐውድና ምሥጢር ጠብቀን እንድንረዳ ታስተምረናለች፡፡

የአምላክ እናት መገለጥ!

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ‹‹በዓለ ደብረ ምጥማቅ›› አደረሳችሁ!

አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለ መታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁላችንም ታላቅ በዓልን እናደርጋለን።

ደብረ ዘይት፡- ዳግም ምጽአት

በመዋዕለ ስብከቱ ስለ ዳግም ምጽአቱና ምልክቶቹ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ በዝርዝር በደቀ መዛምርቱ በኩል አሳውቆናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡…

ነቢዩ ሶምሶን

ሶምሶንም “ከፍልስጥኤማውያን ጋር ልሙት” አለ፤ ተጎንብሶም ምሰሶቹን በሙሉ ኅይሉ ገፋ፤ ቤቱም በውስጡ በነበሩት በመኳንንቱም በሕዝቡም ሁሉ ላይ ወደቀ፤ በሞቱም የገደላቸው ሙታን በሕይወት ሳለ ከገደላቸው በዙ። ወንድሞቹም የአባቱ ቤተ ሰቦችም ሁሉ ወረዱ፤ ይዘውም አመጡት በጾርዓና በኤሽታኦል መካከል ባለው በአባቱ በማኑሄ መቃብር ቀበሩት፤ እርሱም በእስራኤል ላይ ሃያ ዓመት ፈረደ።

በዓለ ደብረ ቁስቋም

በከበረች በኅዳር ስድስት ቀን የምናስበው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከተወደደ ልጇ ከመድኃኒዓለም፣ ከአረጋዊው ዮሴፍ እና ሰሎሜ ጋር ከስደት መመለስ እንዲሁም በቁስቋም ተራራ መገኘት ታላቅ በዓል ነው፡፡

ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ

ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ፣ የዜማ ደራሲና ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ድንቅ ተጋድሎን ፈጽሞ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም የገባበት ዕለት ግንቦት ፲፩ የከበረች እንደመሆኗ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡