ቅድስት አፎምያና ባሕራን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዐዋጅ ታውጀው ከሚጾሙ አጽዋማት አንዱ የሆነው ጾመ ሐዋርያት የሚጾምበት ወቅት ላይ ነንና ይህን ጾም እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችንን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን ከተቀበሉ በኋላ ወደ አገልግሎት ከመሄዳቸው በፊት ጾምን ጾመዋል፤ ይህን ጾም ምእመናን በየዓመቱ በዓለ ኀምሳ ከተከበረ ማግስት ጀምሮ እስከ ሐምሌ አምስት ቀን ድረስ እንጾመዋለን፤ ልጆች! እንግዲህ እኛም እንደ አቅማችን ይህንን ጾም መጾም ይገባናል፤ በዘመናዊ ትምህርታችሁም ከፈተና በፊት በርትታችሁ በማጥናት ፈተናውን በደንብ መሥራት ይገባችኋል ፤ መልካም! ለዛሬ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እንማራለን፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ቅዱሳን መላእክት ከእግዚአብሔር ተልከው እኛን የሚጠብቁን ናቸው፤ መልካም ስንሠራ ችግር በገጠመን ጊዜ በጸሎት ስንማጸናቸው ፈጥነው በመምጣት ከዚያ መከራ ያወጡናል፤ ከእግዚአብሔር አማልደው ምሕረትን ያሰጡናል፡፡ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ከመከራ ካዳናቸው መካከል ሁለቱን ታሪክ አንሥተን ለዛሬ እንማራለን፡፡

ምጽዋት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ እንዲሁም ለበዓለ ኀምሳ አደረሳችሁ! ለአባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የወረደበትን በዓለ ኀምሣ ባከበርን ማግስት ጾመ ሐዋርያት ይገባል፡፡ አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን ከተቀበሉ በኋላ ጥበብ ማስተዋሉን አግኝተው በእምነት ጸንተው የምሥራቹን ወንጌል ለማስተማር ከመሄዳቸው በፊት ጾምን ጾመዋል፡፡ ይህን ጾም ሁል ጊዜ ከበዓለ ኀምሳ ማግሥት ጀምሮ እስከ ሐምሌ አምስት ድረስ እንጾመዋለን፡፡

በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዐዋጅ ከሚጾሙ ሰባቱ አጽዋማት አንዱ ይህ ጾመ ሐዋርያት ወይም በተለምዶ የሰኔ ጾም እየተባለ የሚጠራው ነው፤ እኛም በአቅማችን ይህንን ጾም ልንጾም ይገባናል፤ ከአባቶቻችንን ቅዱሳን ሐዋርያት በረከትን ለማግኘት፣ ጾሙን እንጽም፤ በዘመናዊ ትምህርታችን ትምህርት ጨርሰን የማጠቃለያ ፈተና የምንፈተንበት ወቅት ነውና በርትተን እናጥና ፤ በመጪው ክረምትም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመገኘት መንፈሳዊ ትምህርትን ለመማር ከአሁኑ እናቅድ (እንዘጋጅ) መልካም! ውድ ልጆች! ለዛሬ የምንማረው ስለ “ምጽዋት” ነው፡፡

ተስፋ መንግሥተ ሰማያት!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በዓለ ኀምሳን እንዴት አያሳለፋችሁ ነው? በዓለ ዕርገትም እየደረሰ ነውና በዓሉን ለማክበር መዘጋጀት ያስፈልጋል! ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከማረጉ በፊት በተለያየ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት እየተገለጠላቸው ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ያስተምራቸው ነበር፡፡ በዚህም መሠረት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስናገለግል በሥርዓት ነው፡፡ በትምህርታችንም መበርታት እንዳለብን እንረዳለን፡፡ የፈተና ወቅት እየደረሰ በመሆኑ ከዚያ በፊት በርትተን በማጥናት ዕውቀት አግኝተን ከክፍል ወደ ቀጣይ ክፍል በጥሩ ውጤት መሸጋገር ይገባናል፤ መልካም ልጆች! ለዛሬ ስለ ተስፋ መንግሥተ ሰማያት እንማራለን፡፡

‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› (መክብብ ፫፥፩)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የትንሣኤን በዓል ወቅት (በዓለ ኀምሳን) እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? በሰንበት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ እያስቀደሳችሁ እንደሆነ ተስፋችን እሙን ነው! የአካዳሚ (ዘመናዊ) ትምህርትስ ጠንክራችሁ እየተማራችሁ ነውን! የዓመቱ ትምህርት የሚያበቃበት ጊዜ እየደረሰ ነው! አንዳንዶች ፈተና የምትፈተኑበት ጊዜው በጣም ደርሷል፡፡ በርትታችሁ በመማር፣ በማጥናት ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ አለባችሁ፡፡

ልጆች! ያላችሁበት ወቅት ዓለማችን ከብዙ ሥልጣኔ ደረጃ የደረሰችበት ነው። ታዲያ እናንተም ከዚህ እኩል እንድትራመዱ በርትታችሁ በመማር ችግር ፈቺ፣ መፍትሔ አምጪ መሆን አለባችሁና በርቱ! ባለፈው ትምህርታችን ስለ ሰላም ተምረን ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለ “ጊዜ” እንማራለን! መልካም!

ሰላም!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ዐቢይ ጾም (ጾመ ክርስቶስ) ጨርሰን በዓለ ትንሣኤን እያከበርን ነው፤ በዓሉን እንዴት እያከበራችሁ ነው? የትንሣኤ በዓል ነጻነታችንን አግኝተን ትንሣኤ እንዳለን የተበሠረበት በዓላችን ነውና ታላቅ በዓል ነው፡፡

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶ ሞትን ድል አድርጎ በመነሣቱ ትንሣኤያችንን አበሠረን፤ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለን ዐወቅን፡፡ ታዲያ በጾሙ ወቅት እናደርገው እንደነበረው በጸሎት መበርታትና በመንፈሳዊ አገልግሎት መሳተፍ አለብን፤

በዘመናዊ ትምህርታችን መበርታት እንዳለብንም መዘንጋት አይገባም፡፡ አሁን ያለንበት ጊዜ ትምህርቱ መገባደጃ ወቅት ስለሆነ ከፈተና በፊት በርትተን በማጥናት ዕውቀትን አግኝተን ከክፍል ክፍል በጥሩ ውጤት መሸጋገር ይገባናል፤ መልካም! ለዛሬ ከበዓለ ትንሣኤ ጋር በተያያዘ ስለ ሰላም እንማራለን፡፡

ይቅርታ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው የዐቢይ ጾም ሁዳዴ (ጾመ ክርስቶስ) ስድስተኛውን ጨርሰን ስምንተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ላይ እንገኛለን፡፡ በአቅማችሁ በመጾም በጸሎት በርቱ!

ቤተ ክርስቲያንም ሄዳችሁ መንፈሳዊ ትምህርትን መማር አትዘንጉ! ዘመናዊ ትምህርታችሁንም ቢሆን በርትታችሁ ተማሩ! የሁለተኛው መንፈቀ ዓመት እየተገባደደ ነው! በርትታችሁ አጥኑ! ያልገባችሁን ጠይቁ! አብዛኛውን ጊዜያችሁን በትምህርታችሁ ላይ ትኩረት አደርጉ!፤ መልካም! በዛሬው ክፍለ ጊዜ  “ይቅርታ” በሚል ርእስ እንማራለን፡፡

‹‹በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር›› (ዘፀ.፳፥፲፮)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ዐቢይ ጾም (ጾመ ክርስቶስ) አምስተኛው ሳምንት ላይ እንገኛለን፤ በአቅማችሁ በመጾም በጸሎት እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው፤ በሰንበት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ማስቀደስና መንፈሳዊ ትምህርትን ከመማርም መዘንጋት የለብንም!

በእግዚአብሔር ቤት ስናድግ እንባረካለን፤ አምላካችንም ጥበቡንና ማስተዋሉን ያድለናል፤ በጥሩ ሥነ ምግባር አድገን፣ ለራሳችን ለቤተሰቦቻችን እንዲሁም ለአገራችን መልካም የምንሠራም እንሆናለን፡፡ በዘመናዊ ትምህርታችሁም በርትታችሁ መማር ይገባል፡፡ የሁለተኛ መንፈቀ ዓመት እየተገባደደ ነውና በርትታችሁ ትማሩ ዘንድ አጥኑ፤ ያልገባችሁን ጠይቁ፤ አብዛኛውን ጊዜያችሁን በትምህርታችሁ አተኩሩ፡፡ መልካም! በዛሬው ትምህርታችን ሐሰት (ውሸት) በሚል ርእስ እንማራለን፡፡

‹‹የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት… ነው›› (ገላ.፭፥፳፪)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ጾመ ሁዳዴ (ጾመ ክርስቶስ) ሁለተኛው ሳምንት ላይ እንገኛለን፡፡ እሑድ ከወላጆቻችን ጋር ቤተ ክርስቲያን በመሄድ እያስቀደስን ነው አይደል? እንደ አቅማችን ደግሞ መጾምም አለብን! ከዚህ ቀደም ከምንጸልየው ጸሎት በተጨማሪ ጨምረን ልንጸልይም ይገባል!

በትምህርታችሁም በርቱና ተማሩ! ወላጆቻችን ከእኛ በጣም ብዙ ነገር ይጠብቃሉ፤ ጥሩ ውጤት እንድናመጣና ወደፊት ትልቅ ደረጃ እንድንደርስም ይመኛሉ፤ ታዲያ እኛ ስንፍናን አርቀን፣ ጨዋታን ቀንሰን፣ በርትተን በመማርና በማጥናት ጎበዝ ልጆች መሆን ይገባናል፤ መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ስለ መታዘዝ ተምረን ነበር፤ አሁን ደግሞ ስለ ትዕግሥት እንማራለን፡፡

‹‹ልጆች ሆይ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ›› (ኤፌሶን ፮፥፩)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የሁለተኛው መንፈቅ የትምህርት ዘመን እንዴት ነው? ከቀደመው ይልቅ የበለጠ ጠንክራችሁ በመማር ዕውቀትን በመሸመት ጥሩ ውጤትን ለማምጣት እየጣራችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው!

ልጆች! ዐቢይ ጾምን አንድ ብለን እየጀመርን ነው፤ እንደ ዐቅማችሁ ለመጾም እንደምትጥሩም እምነታችን ነው፤ በርቱ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መንፈሳዊ ትምህርትንም መማርም እንዳትዘነጉ፤ መልካም! ልጆች ለዛሬ ስለ መታዘዝ እንማራለን፡፡

‹‹እግዚአብሔር ፍቅር ነው›› (፩ኛ ዮሐ.፫፥፱)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ አጋማሽ ፈተናስ እንዴት ነበር? መቼም በርትቶ ሲማርና ሲያጠና ለነበረ ተማሪ ፈተናው እንደሚቀለው ተስፋ አለን፤ ጎበዝ ተማሪ የሚያጠናው ፈተና ሲደርስ ብቻ አይደለምና! መምህራን ሲያስተምሩ ተግቶ በአግባቡ የሚከታተል ያልገባውን የሚጠይቅ፣ መጻሕፍትን የሚያነብ የበለጠ ዕውቀት ለማግኘት ተግቶ የሚያጠና ነው!

ታዲያ እንደዚህ አድርጎ ትምህርቱን የሚከታተል ጥሩ ውጤትን ያመጣል! እንግዲህ በተለያየ ምክንያት በግማሽ ዓመቱ ፈተና በደንብ ያልሠራችሁ በቀሪው የትምህርት ዘመን በርትታችሁ በማጥናት ዕውቀትን እንድታገኙና ጥሩ ውጤት እንድታመጡ አደራ እንላለን!

ልጆች! ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁም ጎበዞች መሆን አለባችሁ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ተማሩ! መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ‹‹ተስፋ››  በሚል ርእስ  ስለ ተስፋ ተምረናል፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ፍቅር እንማራለን!