‹‹እግዚአብሔር ፍቅር ነው›› (፩ኛ ዮሐ.፫፥፱)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዓመቱ አጋማሽ ፈተናስ እንዴት ነበር? መቼም በርትቶ ሲማርና ሲያጠና ለነበረ ተማሪ ፈተናው እንደሚቀለው ተስፋ አለን፤ ጎበዝ ተማሪ የሚያጠናው ፈተና ሲደርስ ብቻ አይደለምና! መምህራን ሲያስተምሩ ተግቶ በአግባቡ የሚከታተል ያልገባውን የሚጠይቅ፣ መጻሕፍትን የሚያነብ የበለጠ ዕውቀት ለማግኘት ተግቶ የሚያጠና ነው!

ታዲያ እንደዚህ አድርጎ ትምህርቱን የሚከታተል ጥሩ ውጤትን ያመጣል! እንግዲህ በተለያየ ምክንያት በግማሽ ዓመቱ ፈተና በደንብ ያልሠራችሁ በቀሪው የትምህርት ዘመን በርትታችሁ በማጥናት ዕውቀትን እንድታገኙና ጥሩ ውጤት እንድታመጡ አደራ እንላለን!

ልጆች! ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁም ጎበዞች መሆን አለባችሁ! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ተማሩ! መልካም! ባለፈው ትምህርታችን ‹‹ተስፋ››  በሚል ርእስ  ስለ ተስፋ ተምረናል፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ፍቅር እንማራለን!

‹‹…እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ…›› (፩ኛ ቆሮ.፲፫፥፲፫)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንዲሁም በዓለ ጥምቀቱን እንዴት አክብራችሁ አሰለፋችሁ? እነዚህ በዓላት ከጌታችን ዐበይት በዓላት መካከል የደስታ በዓላችን ናቸው፡፡ ዘመናዊ ትምህርትስ እንዴት ነው? እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው!

የግማሽ ዓመት ትምህርት ተጠናቆ ፈተና እየተፈተናችሁ ያላችሁ እንዲሁም ደግሞ ለፈተና ዝግጁ የሆናችሁ ተማሪዎቸ አላችሁ፤ ትምህርት ከተጀመረ ጊዜ አንሥቶ መምህራን ሲያስተምሩ በደንብ የተከታተለ፣ የተሰጠውን የቤት ሥራ የሠራ እንዲሁም ያልገባውን እየጠየቀ የተረዳ፣ ያጠና ተማሪ ፈተናውን በቀላል ይሠራዋል! እናንተም እንደዚህ እንደምትሆኑ ተስፋችን እሙን (የታመነ) ነው፡፡ በርቱና ተማሩ! ፈተናውንም በተረጋጋ ሁኔታ ሆናችሁ ሥሩ፡፡ መልካም! ለዛሬ “ተስፋ” በሚል ርእስ እንማራለን፡፡

የቱን ታስታውሳላችሁ? የጥያቄዎቹ ምላሾች

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ! ነቢያት በብሉይ ኪዳን “አቤቱ ከሰማያት ወርደህ፣ ተወልደህ አድነን” ብለው የተነበዩት ትንቢት ተፈጽሞ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደበትን ቀን በድምቀት እናከብር ዘንድ ይገባል፡፡

ልጆች! ለዛሬ “የቱን ታስታውሳላችሁ?” በሚለው ላቀረብንላችሁ ጥያቄዎች ምላሾቹን ይዘን ቀርበናል፡፡ አንብባችሁ ምላሽ የሰጣችሁ በርቱ! ያልመለሳችሁ ደግሞ በቀጣይ በምናዘጋጀው ጥያቄና መልስ ተሳተፉ!

የቱን ታስታውሳላችሁ?

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ ነውን? የምትማሩትን ትምህርት እያጠናችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው፤ በርቱ! ልጆች ለዛሬ ይዘንላችሁ የቀረንበው ባለፉት በተከታታይ ሳምንታት ስንማማረው ከነበረው የአማላጅነት ትምህርት ካነበበችሁት (ከተማራችሁት) መካከል “የቱን ታስታውሳላችሁ” በሚል ርእስ ጥያቄዎችን ነው፡፡ በጥንቃቄ አንብባችሁ መልሶቻችሁን በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ!

የቅዱሳን አማላጅነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለጾመ ነቢያት (ለገና ጾም) አደረሳችሁ! ጾመ ነቢያት አባቶቻችን ነቢያት አምላካችን ተወልዶ ያድነን ዘንድ የጾሙት ጾም ነው፤ እኛ ደግሞ ከሰማያት ወርዶ፣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ አድኖናል ስንል ውለታውንና ፍቅሩን እያሰብን እንጾማለን!

በዘመናዊ ትምህርታችሁ የዓመቱን አንድ አራተኛ (ሩቡን የትምህርት ዘመን) ጨረሳችሁ አይደል! መቼም ከነበራችሁ ዕውቀት እንደጨመራችሁ ተስፋ እናደርጋለን! በርትታችሁ ተማሩ እሺ! መልካም!

ባለፈው ተከታታይ ትምህርታችን ስለ አማላጅነት ምንነት፣  ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ስለ ቅዱሳን መላእክት አማላጅነት በተወሰነ መልኩ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችንን አማላጅነት እንማራለን! ተከታተሉን!

የቅዱሳን መላእክት አማላጅነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁልን?! በፈቃደ እግዚአብሔር አዲሱን ዓመት ከተቀበልን ሁለት ወራትን አሳልፈን ሦስተኛውን ጀምረናል! ለዚህ ያደረሰን አምላክ ይመስገን! ለመሆኑ ትናንት ከነበረው ማንነታችሁ ላይ ምን ለውጥ አመጣችሁ? በዘመናዊ ትምህርትስ ምን ያህል ዕውቀትን ሸመታችሁ? በመንፈሳዊ ሕይወታችሁስ በሥነ ምግባር ምን ያህል ለውጥ አመጠችሁ? በርትታችሁ መማር ይገባል፤

….ባለፈው ተከታታይ ትምህርታችን ስለ አማላጅነት ትርጉም እንዲሁም ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ተምረን ነበር፡፡ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ ስለ ቅዱሳን መላእክት አማላጅነት እንማራለን! መልካም!

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? በርትታችሁ እየተማራችሁ ነውን? ጥናቱንም ከወዲሁ ጀምሩ! አዲሱን ዓመት ከተቀበልን ሁለት ወራትን አስቆጥረናል፤ ታዲያ በእነዚህ ጊዜያት በዘመናዊ ትምህርታችን ከነበረን ዕውቀት ምን ያህል አዲስ የማናውቀውን ነገር ዐወቅን? አንዳንድ ትምህርት ቤት የሙከራ ፈተና ጀምረዋል፤ ታዲያ እንዴት ነበር የመመዘኛው ፈተና? ጥሩ ውጤት እንዳስመዘገባችሁ ተስፋችን ነው! መልካም!

ባለፈው ትምህርታችን ስለ አማላጅነት በመጠኑ ተምረናል፤ ለዛሬ ደግሞ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት እንማራለን፤ ተከታተሉን!

አማላጅነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? በርትታችሁ እየተማራችሁ ነውን? ጥናቱንም ከወዲሁ ጀምሩ! ያልገባችሁንም ጠይቁ! መንፈሳዊ ትምህርትንም በዕረፍት ቀናችሁ ተማሩ፤

ወደፊት ለመሆን የምትፈልጉትን ለመሆን አሁን በርትታችሁ ተማሩ! ቤት ስትገቡ የቤት ሥራችሁን ብቻ ሳይሆን መሥራት ያለባችሁ የተማራችሁትንም መከለስ ነው! ከዚያም ያልተረዳችሁትን መምህራችሁን ጠይቁ፤ መልካም!

ባለፈው ትምህርታችን ጥያቄዎች አቅርበንላችሁ ምላሶቹን ልካችሁልን ነበር፤ እኛም ትክክለኛ የሆኑትን ምላሾች ነግረናቹኋል፤ ለዛሬ ደግሞ “አማላጅነት” በሚል ርእስ እንማራለን! ተከታተሉን!

የጥያቄዎቹ ምላሾች

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? አዲሱ ዓመት እንዴት ነው? ዘመን መለወጫን አከበርን፤ ከዚያም የመስቀልን በዓል አከበርን፤ ደስ ይላል አይደል! አሁን ደግሞ ትምህርት ጀምራችኋልና መበርታት ይገባል፡፡ እንግዲህ ከአሁኑ ጀምራችሁ መምህራን የሚሰጧችሁን ትምህርት በንቃት ተከታተሉ! መጻሕፍትን አንብቡ፤ ምክንያቱም አሁን ካላጠናችሁ በኋላ ፈተናዎችን ማለፍ ይከብዳችኋል!

ታዲያ ልጆች! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርንም እንዳንዘነጋ! በሰንበት ሄደን በመማር በሥነ ምግባር ያጌጠ፣ በሃይማኖቱ የጸና ጎበዝ ተማሪ ሆኖ ማደግ ያስፈልጋል፤ መልካም! ዛሬ  ባለፈው ለጠየቅናችሁ ጥያቄዎች ምላሹቹን እንነግራችኋለን! አንብባችሁ ምላሽ የሰጣችሁ በርቱ! ያልመለሳችሁ ደግሞ በቀጣይ በምናዘጋጀው ጥያቄና መልስ ተሳተፉ!

የቱን ታስታውሳላችሁ?

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አሸጋገራችሁ! አዲሱን ዓመት ከተቀበልን ሳምንታትን አስቆጥረን ወር ሊሞላን ጥቂት ቀናት ብቻ ቀሩን! አዲሱ የትምህርት ዘመን እንዴት ነው? ትምህርት ጀመራችሁ አይደል? በርቱ!

ታዲያ ልጆች! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርንም እንዳንዘነጋ! በሰንበት ሄደን በመማር በሥነ ምግባር ያጌጠ፣ በሃይማኖቱ የጸና ጎበዝ ሆነን ማደግ አለብን፤ መልካም! ለዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው “የቱን ታስታውሳላችሁ” በሚል ርእስ እስከ ዛሬ ትማሩት ከነበረው የተወሰነ ጥያቄዎችን አዘጋጅተን ነው፤ ምላሽችሁን ደግሞ በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ!