የቱን ታስታውሳላችሁ?
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና ዕርገት መታሰቢያ ለሆነው ጾመ ፍልሰታ አደረሳችሁ፡፡ ልጆች! በየዓመቱ በጉጉት የምንጠብቃት ጾመ ፍልሰታን እንደ አቅማችን በመጾምና በመጸለይ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤዛዊተ ዓለም በረከትን መቀበል ይገባናል፤ ልጆች! በጾመ ፍልሰታ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ፣ ትምህርት በመማር፣ በማስቀደስ፣ መልካም ምግባራትን በመፈጸም መሳተፍ አለብን፡፡
ልጆች! በዛሬ “የቱን ታስታውሳላችሁ?” መርሐ ግብራችን ባሳለፍነው ዓመት ስንማራቸው ከነበሩ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባራት መካከል የተወሰነ ጥያቄን አዘጋጅተንላችኋል፡፡ ከዚህ ቀደም የአስተማርናችሁን ትምህርት በደንብ ከልሷቸው፤ ከዚያም ለጥያቄዎቹ ተገቢውን ምላሽ በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ! እንደተለመደው ጥሩ ውጤት ለሚያመጡ ልጆች ሽማቶችን አዘጋጅተናል፡፡