መልካም አስተዳደር ለሀገር ሰላም

የመልካምነት ሁሉ መገኛ የሆነችው፣ ሰብሳቢያችን፣ አስተማሪያችን፣ ቅድስት ስፍራ፣ የእውነተኛ ሕይወት መገኛ፣ የአምላክ ቤት መቅደሳችን በዚህ ጊዜ ተከፍታለች፡፡ ልጆቿን በስደት፣ በሞትና በኃጢአት በማጣቷ ሰላምን ማግኘት አልቻለችም፡፡ ይህን ሰላም ማግኘት የምትችለውም ልጆችዋን በቤቷ ስትሰበስብና በመልካም አስተዳደር ማኖር ስትችል መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ዛሬም ዘወትርም በጥላዋ ሥር እንድንከለል የምትጠራንም ለዚህ ነው፡፡ በቤቷ፣ በቅድስናው ስፍራ እንድንኖርም ታስተምረናለች፤ ትመከረናለች፡፡

ይህን የአምላካችንም የሰላም ጥሪ መስማትና ወደ ቤቱ መመለስ ደግሞ ከእኛ ይጠበቃል፡፡ የሰላም ባለቤት የሆነው ጌታችን ካለንበት ሥቃይ አውጥቶ፣ ችግራችንን ፈትቶና ከመከራ አውጥቶ በመልካሙ፣ በጽድቁ ጎዳና ይመራናል፤ እውነተኛ መንገድ እርሱ ነውና፤ ‹‹እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ›› እንዲል፡፡ (ዮሐ.፲፬፥፮) ሕዝብ ሰላም ከሆነ ሀገር ሰላም ይሆናል፤ ሀገር ሰላም የምትሆነው ደግሞ የሁሉ ፈጣሪ አምላካችን እግዚአብሔር ሲከበር፣ ሲፈራ፣ ሲመለክና ቤቱ በቅድስና ሲጠብቅ ነው፡፡

፲፫፻፹፮ አዳዲስ አማንያን የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን ማግኘታቸው ተገለጸ!

በደቡብ ኦሞ እና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ዳሰነች ወረዳ ፲፫፻፹፮ አዳዲስ አማንያን በማኅበረ ቅዱሳን የሐዋርያዊ ተልእኮ አስተባባሪነት የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን ማግኘታቸው የተገለጸ ሲሆን ተጠማቂያኑ ባለፉት ወራት መሠረታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት ሲማሩ  ከነበሩ ወገኖች መካከል  መሆናቸው ታውቋል፡፡ ሥርዓተ ጥምቀታቸውም በኦሞ ብሔረ ብፁዓን አቡነ ዜና ማርቆስ ወአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  አንድነት ገዳም ጥር ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ተፈጽሟል።

ለቤተ ክርስቲያን የሚበጅ ብቁ ዜጋ ለማፍራት በልዩ ትኩረትና በንቃት መሥራት እንደሚገባ ተገለጸ!

የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ለትውልድ ማእከል ግንባታ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ በታኅሣሥ ወር ፳፻፲፯ ዓ.ም. ባካሄደው ልዩ መርሐ ግብር ላይ በመሪጌታ ባሕረ ጥበብ ሙጬ “የሉላዊነት ተጽዕኖ በኦርቶዶክስ ላይ” በሚል ርእስ የቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ ለቤተ ክርስቲያን የሚበጅ ብቁ ዜጋ ለማፍራት በልዩ ትኩረትና በንቃት መሥራት እንደሚገባ የሚያመለክት እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ብፁዕ አቡነ አብርሃም እየተዳከመ የመጣው የብራና መጽሐፍ ዝግጅት ዳግም ማንሠራራቱን ገለጹ

ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት በኅዳር ፲፭፤ ፳፻፲፯ ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በአካሄደው የምስጋና መርሐ ግብር ላይ የተገኙት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ባስተላለፉት መልእክት የብራና መጽሐፍት ዝግጅት ረጅም ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ እየተዳከመ የመጣ ቢሆንም ዛሬ ላይ በዚህ መልክ እያደገ መምጣቱ የሚያስደስት መሆኑን አክለው ገልጸዋል፡፡

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ነገን ዛሬ እንሥራ በሚል ርእስ ጀምረን በርካታ ጉዳዮችን የዳሰስንበትን ጽሑፍ በክፍል ከፋፍለን ስናስነብባችሁ ቆይተናል፡፡ ነገን ዛሬ ለመሥራት፣ የነገዋን ቤተ ክርስቲያን የተሻለች ለማድረግ፣ ወደ ቀደመ ክብሯ፣ መታፈሯና መከበሯ ለመመለስ ይቻል ዘንድ ክብረ ምንኩስናን ማጠናከር፣ ገዳማዊ ሥርዓትን መጠበቅ፣ አሁን የሚታዩ ተግዳሮቶችን ማስወገድ የዚህ ትውልድ ግዴታ መሆኑን አንሥተን ክብረ ምንኩስና ነገ የተሻለ እንዲሆን ከቤተ ክርስቲያን የሚጠበቁ እና ከመነኮሳት የሚጠበቁ ጉዳዮችን በክፍል ዘጠኝ አስነብበናችኋል፡፡ ክፍል ዐሥርን (የመጨረሻውን ክፍል) ይዘን ቀርበናል፡፡ መልካም ንባብ!

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ተወዳጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? በክፍል ሰባት እና ስምንት “ምንኩስና ዛሬ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እያጋጠመው ያለውን ተግዳሮት” አንስተን የተወሰኑ ችግሮችን ለማቅረብ ሞክረን ነበር፤ክብረ ምንኩስና ነገ ምን መሆን አለበት? እንዴትስ የተሻለ እናድርገው? የሚለውን በዚህ በክፍል ዘጠኝ ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ!

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ተወዳጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ በሰላም አደረሳችሁ! በክፍል ስድስት ክብረ ምንኩስና ትናንት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የነበረውን ክብርና ሞገስ ያስገኘውን የቅድስና ፍሬና ያሳረፈውን አሻራ፣ በክፍል ሰባት ደግሞ ምንኩስና ዛሬ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እያጋጠመው ያለውን ተግዳሮት አንሥተን የተወሰኑ ችግሮችን ለማቅረብ ሞክረን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ክፍል ስምንትን አቅርበንላችኋልና ተከታተሉን!

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ተወዳጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ!

በክፍል ስድስት “ክብረ ምንኩስና ትናንት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የነበረውን ክብርና ሞገስ ያስገኘውን የቅድስና ፍሬና ያሳረፈውን አሻራ” አንስተን ለመዳሰስ ሞክረናል፡፡

በዚህ በክፍል ሰባት ደግሞ ምንኩስና ዛሬ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እያጋጠመው ያለውን ተግዳሮት ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡ ቀደም ብለን እንደ ተመለከትነው ምንኩስና ከምድራዊው ይልቅ ሰማያዊውን፣ ከሰው ይልቅ የመላእክትን ግብር መምረጥ፣ ፍጹም ሆኖ ፍጹም የሆነችውን መንግሥት ለመውረስ ሁሉን ትቶ መመነን፣ ከሰው ከዓለም መለየት፣ በገዳም በአጽንዖ በአት፣ በግብረ ምንኩስና መወሰን መሆኑን ተረድተናል፡፡ ይሁን እንጅ በዘመናችን ምንኩስና በዘርፈ ብዙ ተግዳሮት ውስጥ ይገኛል፤ የተወሰኑ ችግሮችን ለማሳየት ያህል፡-

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ውድ የእግዚአብሔር ቤተ ሰቦች! እንደምን ሰነበታችሁ? በዚህ ርእስ ቤተ ክርስቲያን ትናንት ለነበራት ድምቀት፣ ዛሬ ለገጠማት ተግዳሮት፣ ነገም ለሚኖራት ማንነት ክብረ ክህነትና ክብረ ምንኩስና የማይተካ አስተዋጽኦ እንዳላቸው እና እነዚህ ሁለት የክብረ ቤተ ክርስቲያን ምሰሶዎች የነገዋን ቤተ ክርስቲያን ሁኔታ ሊወስኑ እንደሚችሉ መንደርደሪያ ሐሳብ አንሥተን በመቀጠልም “ክብረ ክህነት ትናንት እንዴት ነበር? ዛሬስ ምን ሁኔታ ላይ ነው ? ነገስ ምን መሆን አለበት?” የሚሉ ጉዳዮችን ዳስሰን እስከ ክፍል አምስት አብረን ዘልቀናል፡፡ በክፍል ስድስትና ቀጣዮቹ ክፍሎች ደግሞ “ክብረ ምንኩስና ትናንት፣ ዛሬና ነገ ምን ይመስላልና መምሰል አለበት” የሚለውን እናጋራችኋለን፤ አብራችሁን ዝለቁ! መልካም ንባብ!

‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ተወዳጆች እንደምን ሰነበታችሁ? በዚህ ርእስ ባለፉት ተከታታይ አራት ክፍሎች ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ክብረ ክህነት ጽሑፎችን አቅርበንላችኋል፡፡ በዚህም “ክብረ ክህነት ትናንት እንዴት ነበር? ዛሬስ ምን ሁኔታ ላይ ነው?” የሚሉ ጉዳዮችን በጥቂቱ ለማየት ሞክረናል፡፡ በዚህ በክፍል አምስት ደግሞ የነገዋን ቤተ ክርስቲያን የተሻለች ለማድረግ “ክብረ ክህነት ነገ ምን መሆን አለበት” የሚለውን ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡