“ሰውን በአርአያችንና በአምሳላችን እንፍጠር” (ዘፍ.፩፥፳፮)

በዕለተ ዐርብ እግዚአብሔር አራት ፍጥረታትን ፈጠረ፡፡ እነርሱም በእግር የሚሽከረከሩ፣ በክንፍ የሚበሩና በልብ የሚሳቡ፣ በየብስ፣ የሚኖሩ በደመ ነፍስ ሕያዋን የሆኑ ፍጥረታትን ነው፡፡ በመጨረሻም እግዚአ ዓለም ሥላሴ “ሰውን በአርአያችንና በአምሳላችን እንፍጠር” ብለው በነግህ አራቱን ባሕርያተ ሥጋ አምስተኛ ባሕርየ ነፍስን አዋሕደው የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ አድርገው በማዕከለ ምድር በቀራንዮ ፈጠሩት፡፡ (ዘፍ.፩፥፳፮)

ግሩማን ፍጥረታት

ከአዳም ትውልድ ሰባተኛ የሆነው ነቢዩ ሄኖክ ያልተመረመሩ እጅግ አስደናቂ (ግሩማን) ፍጥረታትና አዕዋፍ ስለመኖራቸው ጨምሮ ሲጽፍ “ከዚያም እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ሄድኹ፤ በዚያም ታላላቅ አውሬዎችን አየሁ፤ አንዱ ከሌላው ልዩ ነው፤ የወፎቹም ፊታቸው ይለያያል፤ መልካቸው ቃላቸውም አንዱ ከሌላው ይለዋወጣል” ይላል፡፡ (ሄኖክ ፰፥፳፱)

“እንስሳትን ጠይቅ ያስተምሩህማል፤ የሰማይ ወፎችን ጠይቅ ይነግሩህማል” (ኢዮብ ፲፪፥፯)

በጻድቁ ኢዮብ መጽሐፍ የተጻፈ ኃይለ ቃል ነው፡፡ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በዕለተ ሐሙስ “ውኃ ሕያው ነፍስ ያላቸውን ተንቀሳቃሾች ታስገኝ” በማለት ቃል በተናገረ ጊዜ በልባቸው የሚሳቡ፣ በእግራቸው የሚሽከረከሩ፣ በክንፋቸው የሚበሩ ፍጥረታት ከባሕር ተገኙ፡፡ (ዘፍ.፩፥፳)

በባሕር ከተፈጠሩ ከነዚህ ፍጥረታት የሚበሉና የሚገዙ፣ የማይበሉ የማይገዙም አሉ፡፡ ከባሕር ጸንተው የሚኖሩ አሉ፤ አንድ ጊዜ በየብስ አንድ ጊዜ በባሕር የሚኖሩ አሉ፤ በክንፋቸው በረው ከባሕር ወጥተው የቀሩም አሉ፡፡ (መጽሐፈ ሥነፍጥረት ምስለ አምስቱ አእማደ ምሥጢር፤ ገጽ ፷፤ ሥነ ፍጥረት ክፍል ሦስት ለከፍተኛ የመንፈሳዊ ትምህርት ተማሪዎች የተዘጋጀ ገጽ ፵)

“ለፀሐይም ቀንን አስገዛው፤ ጨረቃንና ከዋክብትንም ሌሊትን አስገዛቸው” (መዝ.፻፴፭፥፰‐፲)

‹‹የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትን ሥራቸውን ዕወቅ፤ ከሁሉ የሚደንቅ ክበባቸውን ከሁሉ የሚበልጥ ብርሃናቸውን ሁሉ ዕወቅ፤ በየወገናቸው የሚያበሩ የሚመላለሱ የእነዚህን የምሳሌያቸውን ሥራ ዕወቅ፤ ሁሉ ጊዜ እርስ በእርሳቸው እንደምንም እንደሚቀራረቡ ዳግመኛም እንደምንም እንደሚራራቁ ዕወቅ…›› (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ባስልዮስ ምዕራፍ ፴፭፥፲፯)

የዕለተ ሠሉስ ፍጥረታት

ዕለተ ማክሰኞ የፍጥረት ሦስተኛ የምስጋና ሁለተኛ ቀን ነች፤ በባሕረ ሐሳብ ቀመር ደግሞ ዕለተ ቀመር ትባላለች፤ በፀሐይ አቆጣጠር ሰባተኛ ቀን ትባላለች፡፡ ዛሬ ግን የምናነሣው በዕለተ ፍጥረት ስለተከናወነባት ክንዋኔ ነው፡፡

የነፋስ ነገር

እግዚአብሔር ያለ ምክንያት የፈጠረው ፍጥረት የለምና ነፋስንም በምክንያት ፈጥሮታል፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ “ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፤ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል፡፡ ቀን ለቀን ነገርን ታወጣለች፤ ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ትናገራለች” በማለት እንደዘመረው ሥነ ፍጥረት አእምሮ ላለው የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን ባሕርያዊ መገለጫዎች ሥራና ፈቃዳት ያስተምራሉ፡፡ (መዝ.፲፰፥፩) ሰውንም ሲፈጥረው ከዐራቱ ባሕርያተ ሥጋ አምስተኛ ባሕርየ ነፍስን አድርጎ በመልኩና በምሳሌው እንደፈጠረው የታወቀ ነው፡፡ (ዘፍ. ፩፥፳፮) እነዚህ አራቱ ባሕርያተ ሥጋ የሚባሉትም ነፋስ፣ እሳት፣ መሬትና ውኃ ናቸው፡፡ በሥነ ፍጥረት ትምህርት እግዚአብሔር ሰውን ከእነዚህ ዐራት ባሕርያት የፈጠረበት ምክንያት በምልዓትና በስፋት ይተነተናል፡፡ በዚህ አጠር ያለ ጽሑፋችንም ከነፋስ ምን እንማራለን? የሚለውን እናነሣለን፡፡

“እግዚአብሔር ኃያል ነኝ ሲል እሳትን ፈጠረ“ (መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት)

ታላቁ የቤተ ክርስቲያናችን አባት ሊቀ መዘምራን ዕቁበ ጊዮርጊስ ሲናገሩ “እግዚአብሔር ኃያል ነኝ ሲል እሳትን ፈጠረ“ ይላሉ፡፡

‹‹ጠፈር ይሁን፤ ውኃም ከውኃ ይለይ›› (ዘፍ.፩፥፮)

እግዚአብሔር በዕለተ ሰኑይ በቀዳሚት ሰዓት ሌሊት ‹‹ጠፈር ይሁን፤ ውኃም ከውኃ ይለይ›› ብሎ ቢያዘው ከዚህ እስከ ብሩህ ሰማይ ሞልቶ የነበረውን ውኃ ከአራት ከፍሎ አንድን እጅ በመካከል ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ከሰሜን እስከ ደቡብ ዘረጋው፡፡ (ዘፍ.፩፥፮) እንደ ቤተ መንግሥት አዳራሽ ወደ ላይ ጠበብ አድርጎ እንደ ብረት አጸናው፤ ይህ የምናየው ሰማይ ነው፤ ጠፈር ይባላል፡፡ ጠፈር ማለትም ሥዕለ ማይ (የውኃ ሥዕል) ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ጠፈርን መፍጠሩ ስለምንድነው? ቢሉ ረቡዕ የሚፈጥረውን ፀሐይን ሊያቀዘቅዝ ሰውም ይህን እያየ ሰማያዊ ርስት እንዳለው እንዲያውቅ ነው፡፡ እጅግም ነጭ ከሆነ ዓይን እየበዘበዘ እያንጸባረቀ ለሰው የደዌ ምክንያት ይሆን ነበርና፡፡ በድስት ያለ ውኃ በሚታጠብ ጊዜ የእሳት ማቃጠል ሲበዛበት እንደሚሰበር ጠፈርም የፀሐይ ማቃጠል ሲበዛበት እንደ ሸክላው በፈረሰ ነበርና እንዲያጸናው ሐኖስን በላይ አደረገለት፡፡ (መጸሐፈ ሥነ ፍጥረት ገጽ ፳-፳፫

ዓለመ ምድር

ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምድር በገነት ወይም በሲኦል ልትመሰል እንደምትችል ያስረዳሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ወርቃማ ዘመናት ተብሎ የሚጠሩትንም በመጥቀስ የተመረጡ ቅዱሳን ነገሥታት የነገሡበት፣ ደጋግ አባቶች የኖሩበት፣ ሊቀ ጳጳሳትና ጳጳሳት እንዲሁም ቀሳውስትና ካህናት በበጎና በመልካም መንገድ ምእመናንን መርተው በቅድስና ሕይወት ለርስተ መንግሥተ ሰማያት ባበቁበት ጊዜ ምድር በገነት ትመሰል እንደነበር ያስረዳሉ፡፡

‹‹ብርሃን ይሁን!›› (ዘፍ.፩፥፫)

በሥነ ፍጥረት መጀመሪያ ቀን ‹‹ብርሃን ይሁን›› በማለት የተናገረው አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ነው፡፡ (ዘፍ.፩፥፫) ‹‹ብርሃን ይሁን›› በማለት በተናገረ ጊዜም ጨለማ ተገፈፈ፡፡ መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት እንደሚነግረን ቅዱሳን መላእክትም ይህ ብርሃን ዕውቀት ሆኗቸው አምላካቸው እግዚአብሔርን ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› በማለት በአዲስ ምስጋና አመሰገኑት፡፡ ‹‹እኔ ፈጣሪያችሁ ነኝ›› ያለ የሰይጣን ክህደትም በብርሃኑ ተጋለጠ፡፡ (ሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት)