ርእሰ ዲያቆናት ወቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ

ጥቅምት ፲፯፤፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት

ርእሰ ዲያቆናት ወቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ የሹመቱ መታሰቢያ ጥቅምት ፲፯ ነው፡፡ ከሰባቱ ዲያቆናት መካከል ቀዳምት የሆነው ቅዱሱን የመረጡት እራሳቸው ሐዋርያት ናቸው፡፡ የስሙ ትርጓሜ “ፋና፣ አክሊል” የሆነ የእግዚአብሔር ልዩ ባለሟል፣ አጋእዝተ ዓለም ሥላሴን በክብሩ ለማየት የበቃ ሰማዕትም ነው፡፡

ፍጹም እምነት ያለው፣ መንፈሳዊ ቅናትን የተመላ እንዲሁም ተአምር የማድረግ ጸጋ የነበረው ቅዱስ ነበረ፡፡ በዘመኑ የሚያስተምራቸው ትምህርቶችም ሆነ ንግግሮቹ መንፈስ ቅዱስ የመላባቸው ስለነበሩ በመቃወም ይከራከሩት የነበሩትን ሁሉ መልስ አሳጥቶአቸዋል፡፡ በዚህም ነበር በቅንአት ተነሣሥተው በሐሳት ምስክር የከሰሱት፡፡ በኋላም ተፈርዶበት በድንግይ ተወግሮ የሰማዕትነትን አክሊል በተወለደበት ዕለት ጥር አንድ ቀን ተቀብሎአል፡፡

የቅዱስ እስጢፋኖስ ጸሎት፣ አማላጅነት እና ተራዳኢነት አይለየን፤ ከበዓሉ በረከት ያሳተፍን፤ አሜን!