• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

ወርኃ መስከረም

መስከረም ለሚለው ቃል መነሻ “ከረመ” የሚለው ግስ ነው፤ ትርጓሜውም “ቀዳማይ፣ ለዓለም ሁሉ መጀመሪያ፣ ርእሰ ክራማት፣ መቅድመ አውራኅ” የሚለውን ያመለክታል፡፡ በሌላ በኩል መስከረም የመጀመሪያ ወር ስም፣ ከዘመነ ሥጋዌ በፊትም ለዓለም ሁሉ የመጀመሪያ ወር ማለት ነው፤ “መስ” የሚለው ቃልም መነሻ መስየ የሚለው ግስ ሲሆን “ምሴተ ክረምት (የክረምት ምሽት) በምሥጢር ደግሞ ፀአተ ክረምት (የክረምት መውጫ)፣ የክረምት ጫፍ መካተቻ፣ የመፀው መባቻ” መሆኑን ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላታቸው ይገልጣሉ፤ (ገጽ ፮፻፲፪) እንዲሁም “መቅድመ አውራኅ (የወራት መጀመሪያ) ርእሰ ክራማት” ይሰኛል ይላሉ፡፡

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰብዓቱ ዓመተ ምሕረት

ርእሰ ዐውደ ዓመት

ለዘመኑ ጥንት ፍጻሜ የሌለው ጌታ የጨለማውን ጊዜ ክረምቱን አሳልፎ፣ ዘመንን በዘመን ተክቶ፣ ምድርን በእህል (በሰብል) ሸፍኖ፣ ድርቀቷን በአረንጓዴ ዕፅዋት አስውቦ፣ ብሩህ ተስፋን በሰው ልጆች ልቡና ያሠርፃል፤ አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር ሰዎች በአዲስ መንፈስና ዕቅድ በአዲስ ሰብእና፣ በዕድሜ ላይ በተጨመረው ሌላኛው ዘመን ዕቅዳቸውን ለማሳካት፣ ምኞታቸውን ለማስመር ታትረው ይነሣሉ፤ የወቅቱ መቀየር በራሱ አዲስ ነገር እንዲያስቡ ያነቃቃል፤ በአዲስ ዓመት መግቢያ (በርእሰ ዐውደ ዓመት) የአጽዋማት መግቢያ፣ የበዓላት መከበሪያ ቀንና ዕለት ይታወጁበታል፤ ባለፈው ዓመት ዘመኑን በስሙ ተሰይሞለት የነበረው ወንጌላዊ ለተረኛው ማስረከቡን ይበሠርበታል፡፡

ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በዕረፍት ጊዜያችሁ ምን እየሠራችሁ ነው? ቤተ ክርስቲያን በመሄድ፣ መንፈሳዊ ትምህርት በመማር እንዲሁም ደግሞ ለዘመናዊ ትምህርታችሁ አንዳንድ ማጠናከሪያ የሆኑ ትምህርቶችን በመማር እያሳለፋችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! ምክንያቱም በጨዋታ ብቻ ማሳለፍ የለብንም!

እንግዲህ አዲሱን ዘመን ልንቀበል በዝግጅት ላይ ነን! ባለፈው የቡሄ ዕለት ወንዶች ልጆች ዝማሬን እየዘመሩ በዓሉን እንዳከበሩት አሁን ደግሞ ተራው የእኅቶቻችን ነው! አበባ አየሽ ሆይ እያልን የፈጣሪያችንን ድንቅ ሥራ የሚገልጡ ዝማሬዎችን እየዘመራችሁ በዓሉን ለማክበር እየተዘጋጃችሁ ነው አይደል? በርቱ!

ታዲያ በአዲስ ዓመት በሚጀመረው ትምህርት በርትታችሁ ለመማር ዝግጅት ማደረጉንም እንዳንረሳ፤ ሌላው ደግሞ ቤተ ክርስቲያን መሄድን መንፈሳዊ ትምህርትን መማርን መቀጠል አለባችሁ፤ ባለፈው ትምህርታችን ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የነፍስና የሥጋን ቁስል (ሕመም) የሚፈውሱ ስለሆኑት ምሥጢረ ንስሐ እና ምሥጢረ ቀንዲል ተምረን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ የአንድነትና የአገልግሎት ጸጋን ስለሚያሰጡን ሁለት ምሥጢራት እንማራለን፤ መልካም!

ወርኃ ጳጉሜን

ወርኃ ጳጉሜን በዓመቱ መጨረሻ የምትገኝ በአገራችን ኢትዮጵያ እንደ ዐሥራ ሦስተኛው ወር የምትቆጠር ናት፤ ወርኃ ጳጉሜን አምስት ቀናት ያሏት ስትሆን በአራት ዓመት አንድ ጊዜ በዘመነ ሉቃስ መውጫ በዘመነ ዮሐንስ መግቢያ ያለው ስድስት ቀን ይሆናል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላታቸው ጳጉሜን እንዲህ ይተረጉሟታል፤ ጳጉሜን ማለት ጭማሪ ተውሳክ፣ አምስት ቀን፣ ከሩብ፣ ከዐውደ ወር ተርፎ በዓመቱ መጨረሻ የተጨመረ ስለሆነ ትርፍ ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት፣ ገጽ ፱፻፭)

‹‹ጻድቃን እኔን ይጠብቃሉ›› (መዝ.፻፵፩፥፯)

በሰማይና ምድር በሚገኙ ፍጥረታት ሁሉ ምስጉን የሆነ እግዚአብሔር የቤተ ክርስቲያንን ውበት እንድንመለከትባቸውና እግዚአብሔርን  ለማመስገን እንድንሰባሰብባቸው ምክንያት አድርጎ ከሰጠን  ቅዱሳን አባቶች መካከል ታላቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንዱ ናቸው፡፡

ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ጾመ ፍልሰታን እንዴት አሳለፋችሁ? ከሕፃን እስከ አዋቂ በአንድነት የሚጾሙት ጾመ ፍልሰታ እንግዴት አበቃ! ሁላችሁም እንደ ዓቅማችሁ በመጾም ስታስቀድሱ እንደ ነበር እናምናለን፡፡ አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ትንሣኤዋን እና ዕርገቷን እንዲመለከቱ ሱባኤ በገቡ ጊዜ እንደባረከቻቸው እኛንም ዛሬ ትባርከናለች፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ዓመቱ እየተገባደደ ነው፤ በአዲስ ዓመት በሚጀመረው ትምህርት በርትታችሁ ለመማር  ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው? ታዲያ በክረምቱ ሰ/ት/ቤት በመሄድ እንማር፤ እንዘምር እንደነበር፣ ትምህርት ሲከፈትም በዕረፍት ቀናችሁ ቤተ ክርስቲያን መሄድን፣ መንፈሳዊ ትምህርትን መማርን መቀጠል አለባችሁ፤ ባለፈው ትምህርታችን ከሰባቱ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የልጅነት ጸጋን አዲስ ሕይወትን የሚያሰጡ ምሥጢራት የሚባሉትን ምሥጢረ ጥምቀት፣ምሥጢረ ሜሮን፣ ምሥጢረ ቁርባን ተመልክተናል፤ ዛሬ ደግሞ የነፍስና የሥጋ ቁስልን (ሕመም) የሚፈውሱ ስለሆኑት ምሥጢረ ንስሐ እና ምሥጢረ ቀንዲል እንማራለን፤ መልካም!

የቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ፍልሰታ መልእክት

መልካሟ ርግብ

ከቀለማት ሁሉ በላይ በሆነው፣ የፍጹምነት መገለጫ፣ ሰማያዊ ክብር በሚገለጽበት በጸአዳ ብሩኅነት ደምቃ፣ የንጽሕናን ሞገስ ተከናንባና አሸብርቃ በሰማይ ትበራለች፡፡ ከውልደቷ ጀምሮ የፈጠራት ይህን ሰማያዊ ጸጋ ሲያላብሳት እርሷም “አሜን” ብላ ተቀብላ ሰማያዊ መናን እየተመገበችና በሰማያት ሠራዊት እየተጠበቀች ከምድር ከፍ ከፍ ብላ መብረርን ለምዳ ከቤተ ሰቦቿ ተለየች፡፡

ነሐሴና በረከቶቹ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ጸጋዎች ባለቤት ናት፡፡ በብዙ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ጸጋዎች የተሞላች ግን ደግሞ በውል ይህን እውነት የማንረዳ ብዙ ዜጎችም ያላት ሀገር ናት፡፡ “አንድ ሰው ጸጋውን የሚያውቀው ሲያጣው ነው” እንደሚባላው መንፈሳዊና ቁሳዊ፣ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ጸጋዎቿን የምንረዳበትና ጠብቀን ተንከባክበን የምንጠቀምበት ዘመን ይመጣ ዘንድ እንመኛለን፡፡

የዚህች ሀገር ልዩ ጸጋዎች ከሆኑት መካከል ወቅቶች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ምክንያቱም የዐሥራ ሦስት ወር ጸጋ የታደለች በክረምትና በበጋ፣ በጸደይና በበልግ በዐሥራ ሦስት ወር ወራት የተዋቀረ፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ተስማሚ ወቅት ያላት ሀገር በመሆኗ ይህ በብዙዎች ዘንድ የማይገኝ ጸጋ ነው፡፡

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ