በመተከል ሀገረ ስብከት ግልገል በለስ 8620 አዳዲስ አማንያን ተጠመቁ

ሚያዝያ 17 ቀን 2008 ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ

እስከዚህ ዕድሜያችን ድረስ ስንጠብቃችሁ ነበር ተጠማቂያኑ፡፡

02gilgel 2በመተከል ሀገረ ስብከት በግልገል በለስ ማእከል ሥር በሚገኙ 3 ወረዳዎች 8620 አዳዲስ አማንያንን ሚያዝያ 15 እና 16 ቀን 2008 ዓ.ም መጠመቃቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ መርሐ ግብር ገለጸ፡፡

በማንዱራ፣ ድባጤ እና ዳንጉ ወረዳዎች የሚገኙት እነዚህ አዳዲስ አማንያን በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት ከሀገረ ስብከቱ፣ ከወረዳ ቤተ ክህነቶች እና ከግልገል በለስ ማእከል ጋር በመተባበር የቅድሰት ቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲማሩ መቆየታቸውን ከማኅበሩ የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ መርሐ ግብር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዩ ፍቅር እንዳላቸው የገለጹት ተጠማቂያኑ እስከዚህ ዕድሜያችን ድረስ ስንጠብቃችሁ ነበር በማለት ሲናፍቁት የነበረው ጊዜ በመድረሱና ፍላጎታቸው በመሳካቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡

የመረጃው ዝርዝር እንደደረሰን እናቀርባለን፡፡