ታህሣሥ 6 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት ላይ በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የአማርኛ ፕሮግራም ዲ/ን ዓባይነህ ካሴ የተሰጡት ቃለ ምልልስ ማኅበሩን የማይወከል መሆኑን ስለማሳወቅ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን።
በማኅበረ ቅዱሳን ያላቸውን ሓላፊነት በመጥቀስ ዲ/ን ዓባይነህ ካሴ ታህሣሥ 6 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት ላይ በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የአማርኛ ፕሮግራም ለቃለ ምልልስ ቀርበው  በወቅታዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ሓሳብ መስጠታቸው ይታወሳል።  ማኅበረ ቅዱሳንን በመወከል  ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫም ሆነ ቃለ ምልልስ መስጠት የሚችሉት የማኅበሩ ሰብሳቢ ወይም ዋና ጸሐፊ ወይም የማኅበሩ ሕዝብ ግኑኝነት ሓላፊ ናቸው፡፡ ስለዚህ  ዲ/ን ዓባይነህ ካሴ  በቃለ ምልልሳቸው የሰጡት አስተያየት የግል አስተያየታቸው መሆኑን በአክብሮት  እንገልፃለን።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
የማኅበረ ቅዱሳን ጽ/ቤት
ታህሣሥ 12 ቀን 2005 ዓ.ም
አዲስ አበባ