የአበባ ወር

መስከረም ፳፮፤፳፻፲፰ ዓ.ም.

ጊዜ የተለያዩ ተፈጥራዊ ኩነቶችን ያስተናግዳል፤ በዓለም ላይ በሚከሰቱ የወቅቶች መፈራረቅም ምድር አንዳንዴ ስትበለጽግ ሌላ ጊዜ ደግሞ ትራቆታለች፡፡ በክረምት ወራት በሚዘንበው ዝናብ ስትረጥብ በበጋ ደግሞ በፀሐይና በሙቀቱ ትደርቃለች፡፡ በዘመነ መጸው በነፋሳት ስትናወጥ ፈክተው የሚያብቡት አበቦች ግን ያስውቧታል፡፡

ቅዱሱ ሰው አባ ጽጌ ድንግል የአበቦችን ዕጹብ ድንቅ ተፈጥሮና የላቀ ዋጋ በማወቁ ሳይሆን አይቀርም ከአበቦች ሁሉ በሚበልጥ አበባ ለምንመስላት ድንግል ማርያም አበቦችን ያበረከተላት፡፡ በዐሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሱት ሊቁ የደረሱት የማኅሌተ ጽጌ ድርሰት ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፭ ቀን ድረስ ባለው ወቅት የእመቤታችን ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ ብሎም ወደ ኢትዮጵያ መሰደድ እና መንከራተት እንዘክርበታለን፡፡

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት፣ አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤አሜን!