አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ
ጥቅምት ፲፫፤፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት
በከበረች ጥቅምት ፲፬ ቀን አቡነ አረጋዊ ተሠወሩ፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ የመጡት ቅዱስ አባታችን ዘጠኙ ቅዱሳን የእግዚአብሔር አገልጋዮችን ኢትዮጵያ እስኪደርሱ ድረስ በመንገድ የመሯቸው እርሳቸው እንደሆኑ መጽሐፈ ስንክሳር ይገልጻል፡፡
የዘንዶ ጅራት በመያዝ ከደብረ ዳሞ ተራራ ላይ የወጡት፣ በዚያም ፍጹም ገድላቸውን የፈጸሙት ቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብለዋል፡፡ ስማቸውን ለሚጠራና መታሰቢያቸውን ለሚያደርግ እንደሚማርላቸውም ተነግሯቸዋል፡፡
ከመምህራቸው ከአባ ዻኩሚስ በተማሩት መሠረትም ለልጆቻቸው መነኰሳት ሥርዓተ ማኅበርን ሠርተውላቸዋል፡፡ ከዚያም በእግዚአብሔር ቸርነት እንደ ነቢያቱ ሄኖክና ኤልያስ ከዚህ ምድር ተሠውረዋል፡፡
የቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ ጸሎት፣ አማላልጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን!!!
ምንጭ፡- መጽሐፈ ስንክሳር ጥቅምት ፲፬