[smartslider3 slider="3"]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአደረጃጀት መዋቅር እንዲጸድቅ በዕንባ ተጠየቀ

 ጥር 6/2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

  • ቅዱሰ አባታችን ለልጆቼ ምን ላውርሳቸው? ሙስናን? የምእመናን ተወካይ

  • የቤተ ክርስቲያኗን አስተዳደር እናስተካክላለን ብለን ከዚህ ደርሰን ወደኋላ እንመለሳለን ማለት ዘበት ነው፡፡ በጭራሽ አይሞከርም!!! ሐቋንም ይዤ እጓዛለሁ!!!  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያስጠናው መዋቅራዊ ለውጥ ቤተ ክርስቲያናችንን ወደ ተሻለ ልማት ያራምዳል፤ ሙስናን ያጠፋል፤ወደ ሌላ በረት የገቡትን በጎች ይመልሳል፤ እኛም የቤተ ክርስቲያን አካል በመሆናችን የተሻለ አገልግሎት እንድንሰጥ የሚያደርገን በመሆኑ በአስቸኳይ ተግባር ላይ እንዲውልልን በማለት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚገኙ ምእመናን ጥር 5 ቀን 2006 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ለቅዱስ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በንግግርና በእንባ ጠየቁ፡፡

tsihuf2003.jpg

የጥናታዊ ጽሑፍ ግብዣ

tsihuf2003.jpg